
ቡታጅራ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- የቡታጅራ ከተማን ገጽታ የሚቀይርና ለኑሮ ተመራጭ የሚያደርግ የ25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ለኢዜአ እንደገለጹት የኮሪደር ልማት ሥራ ከተሞችን ውብ፣ ለኑሮ ምቹና ተወዳዳሪ ለማድረግ ምቹ መደልደል እየፈጠረ ነው።
በቡታጅራ ከተማ በመጀመሪያው ምዕራፍ የግንባታ ሥራ 2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅትም በሁለተኛው ምዕራፍ ከተማዋን ምቹና ለኑሮ ተመራጭ የሚያደርግ የ25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በልማቱ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች እንዲሁም የአረንጓዴና የፋውንቴን ስፍራዎችን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶች መካተታቸውን ጠቁመዋል።

የኮሪደር ልማቱ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ ሲሆን አጠቃላይ ሥራውን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት መታቀዱን ገልጸዋል፡፡
ለሥራው የሚያስፈልገው ገንዘብ ከውስጥ ገቢና ህብረተሰቡን በማስተባበርና በማሳተፍ እንደሚሸፈንም አቶ አብዱ አመልክትዋል።

በከተማው የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ውብና ጽዱ አካባቢ እየፈጠረ መሆኑን የተናገረው ደግሞ የከተማው ነዋሪ ወጣት ጀማል መካ ነው፡፡
እንደወጣቱ ገለጻ ልማቱ ለበርካታ ሰዎች ማረፊያ፣ መዝናኛና ማንበቢያ ስፍራ የፈጠረ ሲሆን ከተማዋንም ለኑሮ ምቹ እያደረጋት በመሆኑ ልማቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።

የቡታጅራ ከተማ ነዋሪ አቶ መቻል ታደሰ በበኩላቸው መንግሥት ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ፅዱ ለማድረግ የጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ የሚበረታታና መጠናከር ያለበት መሆኑን ተናግረዋል።
በከተማው የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ ለእግረኛ እና ለተሽከርካሪ መንገዶችን የለየ በመሆኑ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስ ባለፈ የከተማዋን ገጽታ እየቀየረው መሆኑን ጠቁመዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው የከተማዋን ውበት እየጨመረና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እያነቃቃ መሆኑን ተናግረው፣ ለሥራው ስኬታማነት የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026