
ቡታጅራ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፡- የቡታጅራ ከተማን ገጽታ የሚቀይርና ለኑሮ ተመራጭ የሚያደርግ የ25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ለኢዜአ እንደገለጹት የኮሪደር ልማት ሥራ ከተሞችን ውብ፣ ለኑሮ ምቹና ተወዳዳሪ ለማድረግ ምቹ መደልደል እየፈጠረ ነው።
በቡታጅራ ከተማ በመጀመሪያው ምዕራፍ የግንባታ ሥራ 2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅትም በሁለተኛው ምዕራፍ ከተማዋን ምቹና ለኑሮ ተመራጭ የሚያደርግ የ25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በልማቱ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች እንዲሁም የአረንጓዴና የፋውንቴን ስፍራዎችን ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶች መካተታቸውን ጠቁመዋል።

የኮሪደር ልማቱ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ ሲሆን አጠቃላይ ሥራውን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት መታቀዱን ገልጸዋል፡፡
ለሥራው የሚያስፈልገው ገንዘብ ከውስጥ ገቢና ህብረተሰቡን በማስተባበርና በማሳተፍ እንደሚሸፈንም አቶ አብዱ አመልክትዋል።

በከተማው የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ውብና ጽዱ አካባቢ እየፈጠረ መሆኑን የተናገረው ደግሞ የከተማው ነዋሪ ወጣት ጀማል መካ ነው፡፡
እንደወጣቱ ገለጻ ልማቱ ለበርካታ ሰዎች ማረፊያ፣ መዝናኛና ማንበቢያ ስፍራ የፈጠረ ሲሆን ከተማዋንም ለኑሮ ምቹ እያደረጋት በመሆኑ ልማቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።

የቡታጅራ ከተማ ነዋሪ አቶ መቻል ታደሰ በበኩላቸው መንግሥት ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ፅዱ ለማድረግ የጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ የሚበረታታና መጠናከር ያለበት መሆኑን ተናግረዋል።
በከተማው የተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ ለእግረኛ እና ለተሽከርካሪ መንገዶችን የለየ በመሆኑ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስ ባለፈ የከተማዋን ገጽታ እየቀየረው መሆኑን ጠቁመዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው የከተማዋን ውበት እየጨመረና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እያነቃቃ መሆኑን ተናግረው፣ ለሥራው ስኬታማነት የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026