
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ ዛሬ በቻይና የአለማቀፍ ንግድ ማስፋፊያ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የተመራን ልዑክ ተቀብለን በሁለቱ ሃገራት የንግድ ግንኙነትና ፕሮሞሽን ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገናል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረገች መሆኗንና ከቻይና ጋርም በቀጣይ ይህን ታሳቢ ያደረገ ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረን አስገንዝቤያለሁ ሲሉም ገልጸዋል።
የንግድ ግንኙነቱ ስለሚጠናከርበት ሁኔታም ምክረ ሀሳብ ማቅረባቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ልዑካን ቡድኑ በቆይታቸው ተዘዋውረው በተመለከቱት የለውጥ ውጤቶች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸውልናል ብለዋል።
ቻይና በቀጣይ ሐምሌ በምታዘጋጀው 3ኛው ዓለም አቀፍ ኤክስፖ እንድንሳተፍ ግብዣ አቅርበውልናል ያሉት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረስብ የቻይናን ገበያ ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ ዝግጅት ተደርጎ እንደምንሳተፍ መግባባት ላይ ደርሰናል ሲሉም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026