የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ፖሊሲ እየተገበረች ነው</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ ዛሬ በቻይና የአለማቀፍ ንግድ ማስፋፊያ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የተመራን ልዑክ ተቀብለን በሁለቱ ሃገራት የንግድ ግንኙነትና ፕሮሞሽን ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገናል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረገች መሆኗንና ከቻይና ጋርም በቀጣይ ይህን ታሳቢ ያደረገ ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረን አስገንዝቤያለሁ ሲሉም ገልጸዋል።

የንግድ ግንኙነቱ ስለሚጠናከርበት ሁኔታም ምክረ ሀሳብ ማቅረባቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ልዑካን ቡድኑ በቆይታቸው ተዘዋውረው በተመለከቱት የለውጥ ውጤቶች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸውልናል ብለዋል።

ቻይና በቀጣይ ሐምሌ በምታዘጋጀው 3ኛው ዓለም አቀፍ ኤክስፖ እንድንሳተፍ ግብዣ አቅርበውልናል ያሉት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረስብ የቻይናን ገበያ ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ ዝግጅት ተደርጎ እንደምንሳተፍ መግባባት ላይ ደርሰናል ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026