
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ ዛሬ በቻይና የአለማቀፍ ንግድ ማስፋፊያ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የተመራን ልዑክ ተቀብለን በሁለቱ ሃገራት የንግድ ግንኙነትና ፕሮሞሽን ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገናል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረገች መሆኗንና ከቻይና ጋርም በቀጣይ ይህን ታሳቢ ያደረገ ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረን አስገንዝቤያለሁ ሲሉም ገልጸዋል።
የንግድ ግንኙነቱ ስለሚጠናከርበት ሁኔታም ምክረ ሀሳብ ማቅረባቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ ልዑካን ቡድኑ በቆይታቸው ተዘዋውረው በተመለከቱት የለውጥ ውጤቶች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸውልናል ብለዋል።
ቻይና በቀጣይ ሐምሌ በምታዘጋጀው 3ኛው ዓለም አቀፍ ኤክስፖ እንድንሳተፍ ግብዣ አቅርበውልናል ያሉት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የንግድ ማህበረስብ የቻይናን ገበያ ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ ዝግጅት ተደርጎ እንደምንሳተፍ መግባባት ላይ ደርሰናል ሲሉም ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026