
አዲስ አበባ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የንግድ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡
የኢትዮ-ቻይና የ2025 የኢኮኖሚ እና ንግድ ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ወሀብረቢ እንዳሉት፤ የኢትዮ- ቻይና የኢኮኖሚና ንግድ ፎረም የሁለቱን ሀገራት ለማጠናከር ያግዛል፡፡

በኢትዮጵያና ቻይና መካከል ያለውን በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጎልበት ትብብሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ቻይና የኢትዮጵያ ትልቅ የልማት አጋር በመሆኗ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር የጎላ ሚና እንዳላትም ተናግረዋል፡፡
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ኢትዮጵያን ትልቅ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ አጋዥ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል፡፡
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮ-ቴሌኮም እና የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጋቸውንም አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም የዲጂታል ፋይናንስና ቴክኖሎጂ እድገት የኢትዮጵያን ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ መጠቀም የሚቻልበት ጊዜ አሁን መሆኑን ያመላክታሉ ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የንግድ ትስስርን ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸው፤ የቻይና ካምፓኒዎች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት እድሎችን እንዲጠቀሙ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ኢትዮጵያ በተፈጥሯዊ እና በባህላዊ ሀብቶች የታደለች ሀገር መሆኗን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና የላቀ የንግድና ኢንቨስትመንት አጋሮች መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏ ተጨማሪ የትብብር አቅምን ያሳድጋል ብለዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ግብርና እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ ይበልጥ ተጠናክሮ የሚሰራባቸው የትብብር መስኮች መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር)፣ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ አካታችና ምቹ የኢንቨስትመንት ምህዳር መፍጠሩን ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በአይ ሲ ቲ፣ በቱሪዝም እና ግብርና እንዲሁም በማዕድን ዘርፎች ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዳሏት ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እና ቻይና መካከል ያለው የኢኮኖሚ ትብብር ፈጣን እድገት ላይ መሆኑን ገልጸው፤ የቻይና ባለሀብቶች እድሉን አጠናክረው ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል።
በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ለመሰማራት ለሚፈልጉ ኢንቨስተሮች የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ገልጸዋል፡፡

የቻይና ዓለም አቀፍ ንግድ ማስታወቂያ ምክር ቤት ምክትል ሊቀ መንበር ቼን ጂያንአን በበኩላቸው ኢትዮጵያ በአፍሪካና በቀጣናው ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ጠቅሰዋል።
በኢትዮጵያ እና ቻይና መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ትብብር ትልቅ እድገት እያሳየ መምጣቱንም ገልጸዋል።
በአፍሪካ ፈጣን እድገት የምታስመዘግብ፣ ለሮድ ኤንድ ቤልት ኢኒሼቲቭ ውጤታማነት የጎላ ሚና ያላትና የቻይና ወሳኝ አጋር መሆኗንም አንስተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026