
ደብረ ብርሃን፤ የካቲት 18/ 2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፍ አብዮት እየፈጠረ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ሚኒስቴሩ በደብረ ብርሃን ከተማ ወደ ምርት የተሸጋገሩ አምስት ኢንዱስትሪዎችን መርቀዋል።
በዚሁ ወቅት እንዳሉትም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ እንደ ሀገር ከፍተኛ ለውጥ ተመዝግቧል።

የንቅናቄው መጀመር ወደ ግንባታ ያልገቡት ኢንዱስትሪዎች ወደ ግንባታ እንዲገቡ እና ምርት ያልጀመሩት ደግሞ ወደ ማምረት እንዲገቡ አስችሏል።
በአገር በቀል ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢንዱስትሪው ዘርፍ የሰጠው ልዩ ትኩረት ውጤት እንደሆነም ጠቁመዋል።
በደብረ ብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴ ክልሉ የኢንዱስትሪ ስበት ማዕከል ለመሆን ያለውን ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው በክልሉ በዚህ ዓመት ብቻ 111 በላይ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል።
ክልሉ የማዕድን፣ የቱሪዝም፣ የግብርና፣ የአግሮ ፕሮሰሲንግና ሌሎች ሃብቶች ባለቤት በመሆኑ በቀጣይም ያለውን ጸጋ ተጠቅሞ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት ባለፉት ሶስት ዓመታት 56 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ያስመዘገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ከተማው ማምጣት ተችሏል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የባለሀብቱና የመንግስት ግንኙነት እየተጠናከረ መጥቷል ያሉት አቶ በድሉ፤ ባለፉት ሰባት ወራት ከ120 በላይ ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ጥያቄ አቅርበው እየታየ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ያልተሸጋገሩ ስምንት ባለሃብቶች የተሰጣቸው መሬት መነጠቁን ተናግረዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026