
ደብረ ብርሃን፤ የካቲት 18/ 2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፍ አብዮት እየፈጠረ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ሚኒስቴሩ በደብረ ብርሃን ከተማ ወደ ምርት የተሸጋገሩ አምስት ኢንዱስትሪዎችን መርቀዋል።
በዚሁ ወቅት እንዳሉትም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ እንደ ሀገር ከፍተኛ ለውጥ ተመዝግቧል።

የንቅናቄው መጀመር ወደ ግንባታ ያልገቡት ኢንዱስትሪዎች ወደ ግንባታ እንዲገቡ እና ምርት ያልጀመሩት ደግሞ ወደ ማምረት እንዲገቡ አስችሏል።
በአገር በቀል ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢንዱስትሪው ዘርፍ የሰጠው ልዩ ትኩረት ውጤት እንደሆነም ጠቁመዋል።
በደብረ ብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴ ክልሉ የኢንዱስትሪ ስበት ማዕከል ለመሆን ያለውን ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው በክልሉ በዚህ ዓመት ብቻ 111 በላይ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል።
ክልሉ የማዕድን፣ የቱሪዝም፣ የግብርና፣ የአግሮ ፕሮሰሲንግና ሌሎች ሃብቶች ባለቤት በመሆኑ በቀጣይም ያለውን ጸጋ ተጠቅሞ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት ባለፉት ሶስት ዓመታት 56 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ያስመዘገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ከተማው ማምጣት ተችሏል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የባለሀብቱና የመንግስት ግንኙነት እየተጠናከረ መጥቷል ያሉት አቶ በድሉ፤ ባለፉት ሰባት ወራት ከ120 በላይ ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ጥያቄ አቅርበው እየታየ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ያልተሸጋገሩ ስምንት ባለሃብቶች የተሰጣቸው መሬት መነጠቁን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026