
ደብረ ብርሃን፤ የካቲት 18/ 2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፍ አብዮት እየፈጠረ መምጣቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ሚኒስቴሩ በደብረ ብርሃን ከተማ ወደ ምርት የተሸጋገሩ አምስት ኢንዱስትሪዎችን መርቀዋል።
በዚሁ ወቅት እንዳሉትም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ እንደ ሀገር ከፍተኛ ለውጥ ተመዝግቧል።

የንቅናቄው መጀመር ወደ ግንባታ ያልገቡት ኢንዱስትሪዎች ወደ ግንባታ እንዲገቡ እና ምርት ያልጀመሩት ደግሞ ወደ ማምረት እንዲገቡ አስችሏል።
በአገር በቀል ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢንዱስትሪው ዘርፍ የሰጠው ልዩ ትኩረት ውጤት እንደሆነም ጠቁመዋል።
በደብረ ብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴ ክልሉ የኢንዱስትሪ ስበት ማዕከል ለመሆን ያለውን ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው በክልሉ በዚህ ዓመት ብቻ 111 በላይ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል።
ክልሉ የማዕድን፣ የቱሪዝም፣ የግብርና፣ የአግሮ ፕሮሰሲንግና ሌሎች ሃብቶች ባለቤት በመሆኑ በቀጣይም ያለውን ጸጋ ተጠቅሞ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት ባለፉት ሶስት ዓመታት 56 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ያስመዘገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ከተማው ማምጣት ተችሏል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የባለሀብቱና የመንግስት ግንኙነት እየተጠናከረ መጥቷል ያሉት አቶ በድሉ፤ ባለፉት ሰባት ወራት ከ120 በላይ ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ጥያቄ አቅርበው እየታየ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ያልተሸጋገሩ ስምንት ባለሃብቶች የተሰጣቸው መሬት መነጠቁን ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026