
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን እቅዷን ለማሳካት እየሰራች መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ለአምስተኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ የቴክኒክ ኮሚቴ የመጨረሻ ዝግጅት ላይ ተገኝተን የስራ አቅጣጫ ሰተናል ሲሉ አስፍረዋል።
የቴክኒክ ኮሚቴው በቢሾፍቱ በማካሄድ ላይ በሚገኘው ዝግጅት እ.አ.አ በ2026 በካሜሮን ለሚካሄደው የአለም ንግድ ድርጅት 14ኛው የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያን አባልነት ለማሳካት ያለመ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
በዚህ መሰረት በከፍተኛ ሞራል፣ የሃገር ፍቅርና በሙያ ብቃት ዝግጅት ማድረግና ለተደራዳሪ ቡድኑ አቅም መሆን እንዳለባቸው መግለጻቸውን በጽሑፋቸው አስፍረዋል።
የዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ንጎዚ ኦኮንጆ በቅርቡ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026