አዲስ አበባ ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን እቅዷን ለማሳካት እየሰራች መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ለአምስተኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ የቴክኒክ ኮሚቴ የመጨረሻ ዝግጅት ላይ ተገኝተን የስራ አቅጣጫ ሰተናል ሲሉ አስፍረዋል።
የቴክኒክ ኮሚቴው በቢሾፍቱ በማካሄድ ላይ በሚገኘው ዝግጅት እ.አ.አ በ2026 በካሜሮን ለሚካሄደው የአለም ንግድ ድርጅት 14ኛው የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያን አባልነት ለማሳካት ያለመ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
በዚህ መሰረት በከፍተኛ ሞራል፣ የሃገር ፍቅርና በሙያ ብቃት ዝግጅት ማድረግና ለተደራዳሪ ቡድኑ አቅም መሆን እንዳለባቸው መግለጻቸውን በጽሑፋቸው አስፍረዋል።
የዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ንጎዚ ኦኮንጆ በቅርቡ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025