
አዲስ አበባ ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል የመሆን እቅዷን ለማሳካት እየሰራች መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ለአምስተኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ የቴክኒክ ኮሚቴ የመጨረሻ ዝግጅት ላይ ተገኝተን የስራ አቅጣጫ ሰተናል ሲሉ አስፍረዋል።
የቴክኒክ ኮሚቴው በቢሾፍቱ በማካሄድ ላይ በሚገኘው ዝግጅት እ.አ.አ በ2026 በካሜሮን ለሚካሄደው የአለም ንግድ ድርጅት 14ኛው የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያን አባልነት ለማሳካት ያለመ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
በዚህ መሰረት በከፍተኛ ሞራል፣ የሃገር ፍቅርና በሙያ ብቃት ዝግጅት ማድረግና ለተደራዳሪ ቡድኑ አቅም መሆን እንዳለባቸው መግለጻቸውን በጽሑፋቸው አስፍረዋል።
የዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ንጎዚ ኦኮንጆ በቅርቡ በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026