የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በአማራ ክልል ልማትን በማጠናከር ፍትሃዊ የግብር አስተዳደር ለማስፈን ትኩረት ተደርጓል - አቶ አረጋ ከበደ</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ የካቲት 18/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የሚካሄደውን ሰላምና ልማት አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ፍትሃዊ የሆነ የግብር አስተዳደር ለማስፈን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።

በክልሉ ገቢዎች ቢሮና በፌደራል ገቢዎች ሚኒስቴር የጋራ ትብብር "ግብር፣ ለሀገር ክብር" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀ የግብር የንቅናቄ መድረክ በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።


ርእሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ላይ እንዳሉት በክልሉ ሀብት በማፍራት በማከማቸትና አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመፍጠር ላይ በማተኮር መስራት ይገባል።

ለክልሉ ሰላምና ልማት የሚያስፈልገውን ገቢ ለመሰብሰብና ጥቅም ላይ ለማዋል በሃብት ፈጠራ ማከማቸትና ኢንቨስት ማድረግ ላይ በትኩረት መሰራት ያለበት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም በክልሉ ፍትሃዊ የግብር አስተዳደርን በማስፈን የተረጋጋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ማጠናከር እንደሚገባ አስረድተዋል።

በክልሉ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ሃብት በማፍራት ከሚያገኙት ገቢ የሚጠበቅባቸውን ግብር የሚከፍሉ ምስጉን ባለሃብቶችን ማበረታታት እንደሚገባም ገልጸዋል።

በተጨማሪም የክልሉ ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ እንዲቻል የግብር አስተዳደር ህጉን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባም አስረድተዋል።


የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ በበኩላቸው የዜጎችን የልማት ፍላጎት ተደራሽ ለማድረግና ሰላምን ለማረጋገጥ ግብርን በአግባቡ መሰብሰብና መምራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የሀገራችንን ተጽዕኖ ፈጣሪነት ደረጃ በደረጃ ለማሻሻል በራስ አቅም የተመሰረተ ኢኮኖሚን መገንባት አስፈላጊ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ይህም አገራችን ያላትን የመልማትና የማደግ አቅም ለመጠቀም ያስችላል ብለዋል።

የአገሪቱ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻል እያሳየ ቢሆንም ከሌሎች የሰሃራ በታች አገራት ጋር ሲነጻጸር አሁንም ሰፊ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አስረድተዋል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ክብረት ማሕመድ በበኩላቸው ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ የክልሉ ግብር የመሰብሰብ አቅም በአራት እጥፍ ማደግ እንደቻለ ገልጸው ክልሉ ካለው ሁሉን አቀፍ ጸጋና ሃብት አንጻር ሲታይ ግን አሁንም የሚቀረው ጉዳይ መኖሩን አስረድተዋል።

በክልሉ ባለፉት ሰባት ወራት የተሰበሰበው 31 ቢሊዮን ብር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የአስር ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው መሆኑንም አስረድተዋል።

በንቅናቄ መድረኩ ላይም ለምስጉን ግብር ከፋዮች ለተባባሪ ተቋማትና ውጤታማ ለሆኑ በየደረጃው ለሚገኙ ገቢ ሰብሳቢ ሰራተኞች እውቅና ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026