
ባህርዳር፤ የካቲት 18/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የሚካሄደውን ሰላምና ልማት አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ፍትሃዊ የሆነ የግብር አስተዳደር ለማስፈን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።
በክልሉ ገቢዎች ቢሮና በፌደራል ገቢዎች ሚኒስቴር የጋራ ትብብር "ግብር፣ ለሀገር ክብር" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀ የግብር የንቅናቄ መድረክ በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

ርእሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ላይ እንዳሉት በክልሉ ሀብት በማፍራት በማከማቸትና አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመፍጠር ላይ በማተኮር መስራት ይገባል።
ለክልሉ ሰላምና ልማት የሚያስፈልገውን ገቢ ለመሰብሰብና ጥቅም ላይ ለማዋል በሃብት ፈጠራ ማከማቸትና ኢንቨስት ማድረግ ላይ በትኩረት መሰራት ያለበት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም በክልሉ ፍትሃዊ የግብር አስተዳደርን በማስፈን የተረጋጋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ማጠናከር እንደሚገባ አስረድተዋል።
በክልሉ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ሃብት በማፍራት ከሚያገኙት ገቢ የሚጠበቅባቸውን ግብር የሚከፍሉ ምስጉን ባለሃብቶችን ማበረታታት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በተጨማሪም የክልሉ ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ እንዲቻል የግብር አስተዳደር ህጉን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባም አስረድተዋል።

የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ በበኩላቸው የዜጎችን የልማት ፍላጎት ተደራሽ ለማድረግና ሰላምን ለማረጋገጥ ግብርን በአግባቡ መሰብሰብና መምራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የሀገራችንን ተጽዕኖ ፈጣሪነት ደረጃ በደረጃ ለማሻሻል በራስ አቅም የተመሰረተ ኢኮኖሚን መገንባት አስፈላጊ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ይህም አገራችን ያላትን የመልማትና የማደግ አቅም ለመጠቀም ያስችላል ብለዋል።
የአገሪቱ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻል እያሳየ ቢሆንም ከሌሎች የሰሃራ በታች አገራት ጋር ሲነጻጸር አሁንም ሰፊ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አስረድተዋል።
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ክብረት ማሕመድ በበኩላቸው ከአገራዊ ሪፎርሙ ወዲህ የክልሉ ግብር የመሰብሰብ አቅም በአራት እጥፍ ማደግ እንደቻለ ገልጸው ክልሉ ካለው ሁሉን አቀፍ ጸጋና ሃብት አንጻር ሲታይ ግን አሁንም የሚቀረው ጉዳይ መኖሩን አስረድተዋል።
በክልሉ ባለፉት ሰባት ወራት የተሰበሰበው 31 ቢሊዮን ብር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የአስር ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው መሆኑንም አስረድተዋል።
በንቅናቄ መድረኩ ላይም ለምስጉን ግብር ከፋዮች ለተባባሪ ተቋማትና ውጤታማ ለሆኑ በየደረጃው ለሚገኙ ገቢ ሰብሳቢ ሰራተኞች እውቅና ተሰጥቷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026