ሀዋሳ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል እየተከናወነ ያለው የመስኖ ልማት ገበያ በማረጋጋትና በስራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወተ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የክልሉ ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ፡፡
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አባላት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን እና በሃዋሳ ከተማ የተከናወኑ የመስኖ እና ሌሎች የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል፡፡
በምልከታቸውም የመስኖ ልማት ስራዎች ገበያን ማረጋጋት እና ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠር ያላቸውን ጉልህ ሚና ገልጸዋል።
ከምክር ቤት አባላት መካከል አቶ ሚሊዮን ዮሳ እና ወይዘሮ ኤልሳቤት ፍቼ ለኢዜአ እንዳሉት በግብርናው መስክ የልማት ስራዎች የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።
ለአብነትም መስኖ ልማቱ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚን ለማሳደግና የስራ ዕድል ለመፍጠር ያለውን ጉልህ ሚና አንስተዋል።
ጦም ያደረ ሰፊ መሬትን በመስኖ ማልማት ምርታማነትን መጨመር መቻሉን ጠቅሰው፤ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በማስፋት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
አቶ ታረቀኝ ታምሬ በበኩላቸው የግብርና ልማቱ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ አቅም የሚያሳድግና የህዝቡን ኑሮ የሚያረጋጋ እንደሆነ ጠቁመዋል።
የተጀመሩ የመስኖ ልማት ስራዎች በቀጣይነት እንዲስፋፉ ምክር ቤቱ ክትትሉን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።
የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ዘነበ ዘርፉ፤ የምክር ቤት አባላቱ በሁለት ቡድን በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና በሃዋሳ ከተማ የመስክ ምልከታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
የምክር ቤት አባላቱ ከሪፖርት ባለፈ በተጨባጭ የተሰሩ ስራዎችን በመስክ ምልከታ ለማረጋገጥ ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡
የተጀመሩ የልማት ስራዎች በሁሉም አካባቢዎች እንዲስፋፉና ቀጣይነት እንዲኖራቸው ምክር ቤቱ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባዔውን ነገ ይጀምራል።፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025