
ሀዋሳ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል እየተከናወነ ያለው የመስኖ ልማት ገበያ በማረጋጋትና በስራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወተ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የክልሉ ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ፡፡
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አባላት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን እና በሃዋሳ ከተማ የተከናወኑ የመስኖ እና ሌሎች የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል፡፡
በምልከታቸውም የመስኖ ልማት ስራዎች ገበያን ማረጋጋት እና ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠር ያላቸውን ጉልህ ሚና ገልጸዋል።
ከምክር ቤት አባላት መካከል አቶ ሚሊዮን ዮሳ እና ወይዘሮ ኤልሳቤት ፍቼ ለኢዜአ እንዳሉት በግብርናው መስክ የልማት ስራዎች የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።
ለአብነትም መስኖ ልማቱ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚን ለማሳደግና የስራ ዕድል ለመፍጠር ያለውን ጉልህ ሚና አንስተዋል።
ጦም ያደረ ሰፊ መሬትን በመስኖ ማልማት ምርታማነትን መጨመር መቻሉን ጠቅሰው፤ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በማስፋት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
አቶ ታረቀኝ ታምሬ በበኩላቸው የግብርና ልማቱ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ አቅም የሚያሳድግና የህዝቡን ኑሮ የሚያረጋጋ እንደሆነ ጠቁመዋል።
የተጀመሩ የመስኖ ልማት ስራዎች በቀጣይነት እንዲስፋፉ ምክር ቤቱ ክትትሉን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።
የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ዘነበ ዘርፉ፤ የምክር ቤት አባላቱ በሁለት ቡድን በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና በሃዋሳ ከተማ የመስክ ምልከታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
የምክር ቤት አባላቱ ከሪፖርት ባለፈ በተጨባጭ የተሰሩ ስራዎችን በመስክ ምልከታ ለማረጋገጥ ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡
የተጀመሩ የልማት ስራዎች በሁሉም አካባቢዎች እንዲስፋፉና ቀጣይነት እንዲኖራቸው ምክር ቤቱ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባዔውን ነገ ይጀምራል።፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026