ሮቤ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- በባሌ ዞን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘንድሮ የሚተከል ምርጥ የቡና ችግኝ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የቡና ችግኞቹ ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁና በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ መሆኑም ተመልክቷል።
በጽህፈት ቤቱ የቡና ጥራት ባለሙያ አቶ ሰለሞን ጋረደው ለኢዜአ እንዳሉት፣ በዞኑ እስካሁን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ 36 ነጥብ 2 ሚሊዮን ምርጥ የቡና ችግኝ ለተከላ ተዘጋጅቷል።
የቡና ችግኞቹ የሚተከሉት በዞኑ የቡና አብቃይ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ነባር የቡና ማሳና ከ14 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ አዲስ መሬት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
ምርጥ የቡና ችግኞች ከጅማ፣ መቻራና ሲናና ግብርና ምርምር ማዕከላት የተገኙትን ጨምሮ 15 የተሻሻሉ የአካባቢ ዝርያዎች ያካተቱና በሽታን ተቋቁመው የተሻለ ምርት የሚሰጡ ናቸው።
በአካባቢው ከሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚገባውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የሚተከሉት እነዚህ የቡና ችግኞች በመንግስትና የግለሰብ የችግኝ ጣቢያዎች ላይ እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የተናገሩት።
የቡና ዝርያዎቹ ከነባሩ የአካባቢ ዝርያ በሄክታር በአማካይ የሚገኘውን ሰባት ኩንታል ምርት ወደ 10 ኩንታል የማሳደግ አቅም አላቸው ብለዋል።
በዞኑ አዲዲስ የቡና ችግኞችን ለማስፋፋት እየተደረገ ከሚገኘው ጥረት በተጓዳኝ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ተክሎችን የማደሱ ሥራ ጎን ለጎን እየተሰራ መሆኑንም አስታውሰዋል።
በዚህም በዞኑ ከ1 ሺህ 450 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ያረጃ ቡና የማደስ ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል።
በባሌ ዞን በአሁኑ ወቅት ከ60 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በቡና ተክል የተሸፈነ መሆኑን ከዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025