የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በባሌ ዞን ዘንድሮ የሚተከል ምርጥ የቡና ችግኝ እየተዘጋጀ ነው</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- በባሌ ዞን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘንድሮ የሚተከል ምርጥ የቡና ችግኝ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የቡና ችግኞቹ ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁና በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ መሆኑም ተመልክቷል።


በጽህፈት ቤቱ የቡና ጥራት ባለሙያ አቶ ሰለሞን ጋረደው ለኢዜአ እንዳሉት፣ በዞኑ እስካሁን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ 36 ነጥብ 2 ሚሊዮን ምርጥ የቡና ችግኝ ለተከላ ተዘጋጅቷል።

የቡና ችግኞቹ የሚተከሉት በዞኑ የቡና አብቃይ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ነባር የቡና ማሳና ከ14 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ አዲስ መሬት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።

ምርጥ የቡና ችግኞች ከጅማ፣ መቻራና ሲናና ግብርና ምርምር ማዕከላት የተገኙትን ጨምሮ 15 የተሻሻሉ የአካባቢ ዝርያዎች ያካተቱና በሽታን ተቋቁመው የተሻለ ምርት የሚሰጡ ናቸው።

በአካባቢው ከሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚገባውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የሚተከሉት እነዚህ የቡና ችግኞች በመንግስትና የግለሰብ የችግኝ ጣቢያዎች ላይ እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የተናገሩት።

የቡና ዝርያዎቹ ከነባሩ የአካባቢ ዝርያ በሄክታር በአማካይ የሚገኘውን ሰባት ኩንታል ምርት ወደ 10 ኩንታል የማሳደግ አቅም አላቸው ብለዋል።

በዞኑ አዲዲስ የቡና ችግኞችን ለማስፋፋት እየተደረገ ከሚገኘው ጥረት በተጓዳኝ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ተክሎችን የማደሱ ሥራ ጎን ለጎን እየተሰራ መሆኑንም አስታውሰዋል።

በዚህም በዞኑ ከ1 ሺህ 450 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ያረጃ ቡና የማደስ ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል።

በባሌ ዞን በአሁኑ ወቅት ከ60 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በቡና ተክል የተሸፈነ መሆኑን ከዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026