
ሮቤ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- በባሌ ዞን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘንድሮ የሚተከል ምርጥ የቡና ችግኝ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የቡና ችግኞቹ ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁና በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ መሆኑም ተመልክቷል።

በጽህፈት ቤቱ የቡና ጥራት ባለሙያ አቶ ሰለሞን ጋረደው ለኢዜአ እንዳሉት፣ በዞኑ እስካሁን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ 36 ነጥብ 2 ሚሊዮን ምርጥ የቡና ችግኝ ለተከላ ተዘጋጅቷል።
የቡና ችግኞቹ የሚተከሉት በዞኑ የቡና አብቃይ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ነባር የቡና ማሳና ከ14 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ አዲስ መሬት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
ምርጥ የቡና ችግኞች ከጅማ፣ መቻራና ሲናና ግብርና ምርምር ማዕከላት የተገኙትን ጨምሮ 15 የተሻሻሉ የአካባቢ ዝርያዎች ያካተቱና በሽታን ተቋቁመው የተሻለ ምርት የሚሰጡ ናቸው።
በአካባቢው ከሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚገባውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የሚተከሉት እነዚህ የቡና ችግኞች በመንግስትና የግለሰብ የችግኝ ጣቢያዎች ላይ እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የተናገሩት።
የቡና ዝርያዎቹ ከነባሩ የአካባቢ ዝርያ በሄክታር በአማካይ የሚገኘውን ሰባት ኩንታል ምርት ወደ 10 ኩንታል የማሳደግ አቅም አላቸው ብለዋል።
በዞኑ አዲዲስ የቡና ችግኞችን ለማስፋፋት እየተደረገ ከሚገኘው ጥረት በተጓዳኝ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ተክሎችን የማደሱ ሥራ ጎን ለጎን እየተሰራ መሆኑንም አስታውሰዋል።
በዚህም በዞኑ ከ1 ሺህ 450 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ያረጃ ቡና የማደስ ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል።
በባሌ ዞን በአሁኑ ወቅት ከ60 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በቡና ተክል የተሸፈነ መሆኑን ከዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026