
ሮቤ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- በባሌ ዞን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘንድሮ የሚተከል ምርጥ የቡና ችግኝ እየተዘጋጀ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የቡና ችግኞቹ ከግብርና ምርምር ማዕከላት የተለቀቁና በሽታን በመቋቋም የተሻለ ምርት የሚሰጡ መሆኑም ተመልክቷል።

በጽህፈት ቤቱ የቡና ጥራት ባለሙያ አቶ ሰለሞን ጋረደው ለኢዜአ እንዳሉት፣ በዞኑ እስካሁን የቡና ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ 36 ነጥብ 2 ሚሊዮን ምርጥ የቡና ችግኝ ለተከላ ተዘጋጅቷል።
የቡና ችግኞቹ የሚተከሉት በዞኑ የቡና አብቃይ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ነባር የቡና ማሳና ከ14 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ አዲስ መሬት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
ምርጥ የቡና ችግኞች ከጅማ፣ መቻራና ሲናና ግብርና ምርምር ማዕከላት የተገኙትን ጨምሮ 15 የተሻሻሉ የአካባቢ ዝርያዎች ያካተቱና በሽታን ተቋቁመው የተሻለ ምርት የሚሰጡ ናቸው።
በአካባቢው ከሚያዝያ ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚገባውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የሚተከሉት እነዚህ የቡና ችግኞች በመንግስትና የግለሰብ የችግኝ ጣቢያዎች ላይ እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የተናገሩት።
የቡና ዝርያዎቹ ከነባሩ የአካባቢ ዝርያ በሄክታር በአማካይ የሚገኘውን ሰባት ኩንታል ምርት ወደ 10 ኩንታል የማሳደግ አቅም አላቸው ብለዋል።
በዞኑ አዲዲስ የቡና ችግኞችን ለማስፋፋት እየተደረገ ከሚገኘው ጥረት በተጓዳኝ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ተክሎችን የማደሱ ሥራ ጎን ለጎን እየተሰራ መሆኑንም አስታውሰዋል።
በዚህም በዞኑ ከ1 ሺህ 450 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ያረጃ ቡና የማደስ ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል።
በባሌ ዞን በአሁኑ ወቅት ከ60 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በቡና ተክል የተሸፈነ መሆኑን ከዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026