
አዳማ ፤ የካቲት 20/2017( ኢዜአ)፦ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የልህቀት ማዕከላቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት የሚያስችለውን ስምምነት ከደቡብ ኮሪያው ሳምሳንግ ኩባንያ ጋር ዛሬ ተፈራረመ።
የልህቀት ማዕከላቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀት የሀገሪቷን የኢንዱስትሪ ልማት በዘመናዊ የምርምር ቴክኖሎጂ ውጤቶችና ግኝቶች ለመደገፍ እንደሚያስችለው ተገልጿል።

የተሽከርካሪ መገጣጠሚያ፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ አድቫንስ ማኑፋክቸሪንግና አድቫንስ ማቴሪያል ደግሞ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲደራጁ አምስቱ የዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከላት መሆናቸው ታውቋል።
ለእነዚህ የልህቀት ማዕከላት ዘመኑ የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማሟላት የሚያስችለው ስምምነት ነው ከደቡብ ኮሪያው የሰምሳንግ ቴክኖሎጂ ኩባንያና ኮንሰርቲየም ጋር ዛሬ የተፈራረሙት።
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ለሚ ጉታ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት የልህቀት ማዕከላቱን የምርምር ፓርክ አሁን የዓለም የምርምር ቴክኖሎጂ ደረጃ በደረሰበት የላቦራቶሪ መሳሪያዎች ለማደራጀት የዛሬው ስምምነት ተፈርሟል።
''የላቦራቶሪ ግብዓቱ ግዥ በረዥም ጊዜ ብድር ከደቡብ ኮሪያ በተገኘው 100 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከሰምሳንግ ኩባንያ ጋር ተፈራርመናል'' ብለዋል።
በኩባንያው በኩል የምርምር ላቦራቶሪ መሳሪያዎችን የመገጣጠም ስራ በአንድ ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል።
የሳምሰንግ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኮርፖሬሽን የምስራቅ አፍሪካ ስራ አስኪያጅ ቹልሱን ሀዋንግ በበኩላቸው ኩባንያው የላብራቶሪ ቴክኖሎጂዎችና የምርምር መሳሪያዎችን በቅርቡ የማደራጀት ስራ ይጀመራል ብለዋል።
የልህቀት ማዕከላቱ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የማደራጀት ስራውን እንደሚያጠናቀቅም ገልጸዋል።
ኩባንያው ከመሳሪያዎች መገጣጣም ባሻገር የመብራት፣ ውሃ፣ የውስጥ መስመሮች እና የላቦራቶሪ ማስተዳደር የሚያግዙ ሶፍትዌሮች እንደሚያለማ ተገልጿል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026