የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከላቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ የካቲት 20/2017( ኢዜአ)፦ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የልህቀት ማዕከላቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት የሚያስችለውን ስምምነት ከደቡብ ኮሪያው ሳምሳንግ ኩባንያ ጋር ዛሬ ተፈራረመ።

የልህቀት ማዕከላቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀት የሀገሪቷን የኢንዱስትሪ ልማት በዘመናዊ የምርምር ቴክኖሎጂ ውጤቶችና ግኝቶች ለመደገፍ እንደሚያስችለው ተገልጿል።


የተሽከርካሪ መገጣጠሚያ፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ አድቫንስ ማኑፋክቸሪንግና አድቫንስ ማቴሪያል ደግሞ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲደራጁ አምስቱ የዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከላት መሆናቸው ታውቋል።

ለእነዚህ የልህቀት ማዕከላት ዘመኑ የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማሟላት የሚያስችለው ስምምነት ነው ከደቡብ ኮሪያው የሰምሳንግ ቴክኖሎጂ ኩባንያና ኮንሰርቲየም ጋር ዛሬ የተፈራረሙት።

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ለሚ ጉታ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት የልህቀት ማዕከላቱን የምርምር ፓርክ አሁን የዓለም የምርምር ቴክኖሎጂ ደረጃ በደረሰበት የላቦራቶሪ መሳሪያዎች ለማደራጀት የዛሬው ስምምነት ተፈርሟል።

''የላቦራቶሪ ግብዓቱ ግዥ በረዥም ጊዜ ብድር ከደቡብ ኮሪያ በተገኘው 100 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከሰምሳንግ ኩባንያ ጋር ተፈራርመናል'' ብለዋል።

በኩባንያው በኩል የምርምር ላቦራቶሪ መሳሪያዎችን የመገጣጠም ስራ በአንድ ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል።

የሳምሰንግ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኮርፖሬሽን የምስራቅ አፍሪካ ስራ አስኪያጅ ቹልሱን ሀዋንግ በበኩላቸው ኩባንያው የላብራቶሪ ቴክኖሎጂዎችና የምርምር መሳሪያዎችን በቅርቡ የማደራጀት ስራ ይጀመራል ብለዋል።

የልህቀት ማዕከላቱ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የማደራጀት ስራውን እንደሚያጠናቀቅም ገልጸዋል።

ኩባንያው ከመሳሪያዎች መገጣጣም ባሻገር የመብራት፣ ውሃ፣ የውስጥ መስመሮች እና የላቦራቶሪ ማስተዳደር የሚያግዙ ሶፍትዌሮች እንደሚያለማ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026