አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ በገጠራማው የሀገሪቷ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ሀይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የግሉ ዘርፍ ብርቱ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢትዮጵያ ሶላር ኢነርጂ ልማት ማሕበር የተዘጋጀ ዐውደ ርዕይ ዛሬ በሳይንስ ሙዚዬም ተከፍቷል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት ከዋናው መስመር የራቁና አብላጫው ሕዝብ በሚኖርባቸው የሀገሪቷ ገጠራማ አካባቢዎች አማራጭ የሀይል ምንጮችን በመጠቀም የሃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ጥረት ተደርጓል።
በተለይም በገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ትግበራ በሀገሪቷ ገጠራማ አካባቢዎች ከፀሐይ ኃይል የመነጨ ሃይል ተደራሽ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል በገጠራማው ክፍል በተቋማትና ግለሰቦች ቤት የሶላር ኢነርጂ አማራጭ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን አውስተዋል።
የሀገሪቷን የሀይል ተደራሽነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ግን የግል ዘርፍ ብርቱ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው ያነሱት።
በዕለቱ የተከፈተው ዐውደ ርዕይም በዘርፉ የተሰማሩ የግሉ ዘርፍ ተዋኒያን ትስስርና ቅንጅት ለማጎልበት እንደሚያግዝ አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ሶላር ኢነርጂ ልማት ማሕበር ዋና ዳይሬክተር የምስራች ሲሳይ ፣በገጠራማ አካባቢ ከሶላር የሚመነጭ ኃይልን ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ማሕበሩ የራሱን ተሳትፎ እያደረገ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ የዘርፉ ቴክናሎጂዎችን ለማስተዋወቅና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025