
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ በገጠራማው የሀገሪቷ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ሀይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የግሉ ዘርፍ ብርቱ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢትዮጵያ ሶላር ኢነርጂ ልማት ማሕበር የተዘጋጀ ዐውደ ርዕይ ዛሬ በሳይንስ ሙዚዬም ተከፍቷል።

ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት ከዋናው መስመር የራቁና አብላጫው ሕዝብ በሚኖርባቸው የሀገሪቷ ገጠራማ አካባቢዎች አማራጭ የሀይል ምንጮችን በመጠቀም የሃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ጥረት ተደርጓል።
በተለይም በገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ትግበራ በሀገሪቷ ገጠራማ አካባቢዎች ከፀሐይ ኃይል የመነጨ ሃይል ተደራሽ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል በገጠራማው ክፍል በተቋማትና ግለሰቦች ቤት የሶላር ኢነርጂ አማራጭ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን አውስተዋል።
የሀገሪቷን የሀይል ተደራሽነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ግን የግል ዘርፍ ብርቱ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ ነው ያነሱት።
በዕለቱ የተከፈተው ዐውደ ርዕይም በዘርፉ የተሰማሩ የግሉ ዘርፍ ተዋኒያን ትስስርና ቅንጅት ለማጎልበት እንደሚያግዝ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ሶላር ኢነርጂ ልማት ማሕበር ዋና ዳይሬክተር የምስራች ሲሳይ ፣በገጠራማ አካባቢ ከሶላር የሚመነጭ ኃይልን ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ማሕበሩ የራሱን ተሳትፎ እያደረገ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ የዘርፉ ቴክናሎጂዎችን ለማስተዋወቅና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026