
ሀዋሳ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ) :- በሲዳማ ክልል አምራች ኢንዱስትሪውን በመደገፍ ዘርፉ የሚያስገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡
በክልሉ በሀዋሳ ከተማ በግል ባለሀብት በ80 ሚሊየን ብር የተገነባ የእብነበረድና ግራናይት ፋብሪካ ተመርቆ ወደ ስራ ገብቷል፡፡
የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጎሳዬ ጎዳና በዚህ ጊዜ እንደገለጹት በክልሉ የይርጋለምና ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉትን ጨምሮ ከ1 ሺህ 300 በላይ ኢንዱስትሪዎች ይገኛሉ፡፡
በክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ ዘርፉ የሚያስገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ ያለው ሰላምና ለአምራች ኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆን የጥሬ እቃ አቅርቦት መኖር ዘርፉን የሚቀላቀሉ ባለሃብቶችን ቁጥር እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ለአብነት የዛሬውን ጨምሮ በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከአምስት በላይ አምራች ኢንደስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን አንስተው ይህም የክልሉን ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዋና ዳይሬክተር አለባቸው ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለመደገፍ አዲስ ፖሊሲ ቀርጾ ወደ ስራ ገብቷል፡፡
"ፖሊሲው የግል ባለሃብቶች ዘርፉን እንዲቀላቀሉና መሪ ተዋናይ እንዲሆኑ የሚያደርግ በመሆኑ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ውጤታማነት የተቀናጀ ድጋፍ ያስፈልጋል "ብለዋል፡፡
መንግስት ለአምራች ዘርፉ የሚሰጠውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማሳደግ የፖሊሲ አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጸው የግል ባለሃብቶች ያለውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው በሀገር እድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡
ፋብሪካው በ80 ሚሊዮን ብር ካፒታል ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት የዓለም እብነበረድና ግራናይት ፋብሪካ ባለቤት አቶ ዓለምገና ዘርጋው በበኩላቸው "ለ80 ሰዎች የስራ እድል የሚፈጥር ነው" ብለዋል፡፡
የክልሉ መንግስት ቦታ ከመስጠት ጀምሮ ለፋብሪካው ግብዓት የሚሆኑ እብነበረድና ግራናይት ሃብቶችን በጥናት በመለየት እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከፋብሪካው በሚገኘው ተረፈ ምርት የሳሙናና ቀለም ፋብሪካ የማቋቋም እቅድ እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡
በፋብሪካው የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ውብሸት በቀለ በማሽን ኦፕሬተርነት እየሰራ መሆኑን ጠቅሶ ክህሎቱን የሚያሳድግበት ስልጠና መውሰዱንም ተናግሯል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026