የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የተቀናጀና የተናበበ መረጃ ተደራሽ ማድረግ ከሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ይጠበቃል

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ የካቲት 30/2017 ዓ.ም (ኢዜአ)፦ የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የተቀናጀና የተናበበ መረጃን ተደራሽ ማድረግ እንዲችል ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለፁ።

የፌዴራልና የክልል መንግስት ኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ተቋማት ሃላፊዎች ሀላፊዎችና ባለሙያዎች በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።


የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ መድረኩ ዘርፉን ለማጠናከር የተሻለ አቅም የተፈጠረበት ነው።

የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት ዓላማ መር፣ የተቀናጀ እና የተናበበ መረጃን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችላቸው ገለጻ በመድረኩ መደረጉን ተናግረዋል።

ይህም ዘርፉ እርስ በርስ የሚደጋገፍበት፣ የተቀናጀ የመረጃ ፍሰት ስርዓት እንዲኖር እና የጋራ ጉዳይ ላይ ያተኮሩ ወጥ መልእክቶችን ተደራሽ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል።

ዘርፉ የሚናገር ብቻ ሳይሆን ሕብረ ብሔረዊ አንድነትን ለማጠናከር እንዲሁም የብሔራዊነት ትርክትን ለመገንባት ትልቅ አስተዋጾ እንዲኖረው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ረገድ ሚኒስቴሩ ስልጠናዎችን በመስጠት፣ አስራርና ስታንዳርዶችን በማዘጋጀትና ተፈጻሚነታቸውን በመከታተል የተቀናጀና የተናበበ መረጃ ተደራሽ እንዲሆን በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

የኮሙኒኬሽን ዘርፉ ከሚዲያ ጋር ያለውን ግንኙነት እንዲያጠናከር አስፈላጊ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን አቶ ተስፋሁን አክለዋል።

እንደ ሚኒስትር ደኤታ ገለጻ ባለንበት ዲጂታል ዓለም ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር ዘርፉ የበለጠ አቅሙን ማጠናከር እንዳለበት በመድረኩ አቅጣጫ ተቀምጧል።

የሚዲያ እና ኮሚነኬሽን ዘርፉ ሀሰተኛ መረጃን ከመመከት አንጻር ትክክለኛ መረጃን በተከታታይ ተደራሽ ማድረግ ላይ ሊያተኩር ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።

የግምገማ መድረኩ ተሳታፊዎች በአዳማ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን ጉብኝቱም ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን ተናግረዋል።


በተለይ የአዳማ ከተማን ስማርት ሲቲ በማድረግ በኩል እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህም ከአገልግሎት አሰጣጥ አንጻር ተሞክሮ የሚወሰድበት መሆኑን ገልጸዋል።


በተጨማሪም በአዳማ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የከተማ ግብርና ሥራዎች የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ለማሳካት የሚያግዙ መሆናቸውን ተሳታፊዎች ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025