የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በምዕራብ ጎንደር ዞን ከመስኖ ልማት ከ428 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተገኘ

Mar 10, 2025

IDOPRESS

መተማ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን ከመስኖ ልማት ከ428 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በገንዳውኃ ከተማ የአንደኛ ዙር የበጋ መስኖ ልማት ስራ አፈጻጸም ግምገማና የ2ኛ ዙር የመስኖ ልማትን በተመለከተ ጉብኝት ተካሂዷል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ጤናው ፈንታሁን፤ በዞኑ በአንደኛ ዙር የመስኖ ልማት ከ4 ሺህ 500 በላይ አርሶ አደሮች የተሳተፉበት 2 ሺህ 500 ሄክታር መሬት መልማቱን ገልጸዋል።

ከዚህም ከ428 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን በሁለተኛው ዙርም ከታቀደው በላይ ለማሳካት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አንስተዋል።

የተገኘው ምርት ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው የገበያ ችግር እንዳይከሰትም ከንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ጋር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።


የዛሬው ጉብኝት ዓላማም የአርሶ አደሮቹን የምርት ሁኔታ በመገምገም የገበያ ትስስሩን ለማቀላጠፍ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።

ከመስኖ አምራች አርሶአደሮች መካከል አቶ ጥላሁን የሱፍ፤ ከአራት ሄክታር በላይ መሬታቸውን በመስኖ በማልማት ከ500 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ዘንድሮ የግብአት አቅርቦቱ የተሻለ በመሆኑ ከጠበቁት ባላይ የአትክልት ምርት ማግኘታቸውን ጠቁመውየገበያ ትስስሩ ቀድሞ ባለመፈጠሩ ከሽያጩ ያገኙት ገቢ የምርቱን ያህል አለመሆኑን ተናግረዋል።

ሌላኛው አልሚ አርሶ አደር ሀሰን አልዩ፤ በሶስት ሄክታር መሬት ላይ ካለሙት ሰብል ከ400 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

በመስኖ ልማቱ ለአራት ሰዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ጠቅሰው የገበያ ትስስሩ ፈጥኖ ካልተፈጠረላቸው ለኪሳራ እዳረጋለሁ የሚል ስጋት እንዳላቸው ተናግረዋል።

በስድስት ሄክታር መሬት ላይ አትክልት እያለሙ ያሉት አርሶ አደር ማማር ሙሉጌታ፤ የተገኘው ምርት ከፍተኛ በመሆኑ የገበያ ትስስር ይፈጠርልን ሲሉ ጠይቀዋል።

በዞኑ በ2ኛው ዙር የመስኖ ልማት ከ550 ሄክታር መሬት በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን 138 ሄክታር ማልማት መቻሉ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025