
መተማ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን ከመስኖ ልማት ከ428 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በገንዳውኃ ከተማ የአንደኛ ዙር የበጋ መስኖ ልማት ስራ አፈጻጸም ግምገማና የ2ኛ ዙር የመስኖ ልማትን በተመለከተ ጉብኝት ተካሂዷል።
በምዕራብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ጤናው ፈንታሁን፤ በዞኑ በአንደኛ ዙር የመስኖ ልማት ከ4 ሺህ 500 በላይ አርሶ አደሮች የተሳተፉበት 2 ሺህ 500 ሄክታር መሬት መልማቱን ገልጸዋል።
ከዚህም ከ428 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን በሁለተኛው ዙርም ከታቀደው በላይ ለማሳካት የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አንስተዋል።
የተገኘው ምርት ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው የገበያ ችግር እንዳይከሰትም ከንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ጋር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የዛሬው ጉብኝት ዓላማም የአርሶ አደሮቹን የምርት ሁኔታ በመገምገም የገበያ ትስስሩን ለማቀላጠፍ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
ከመስኖ አምራች አርሶአደሮች መካከል አቶ ጥላሁን የሱፍ፤ ከአራት ሄክታር በላይ መሬታቸውን በመስኖ በማልማት ከ500 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
ዘንድሮ የግብአት አቅርቦቱ የተሻለ በመሆኑ ከጠበቁት ባላይ የአትክልት ምርት ማግኘታቸውን ጠቁመውየገበያ ትስስሩ ቀድሞ ባለመፈጠሩ ከሽያጩ ያገኙት ገቢ የምርቱን ያህል አለመሆኑን ተናግረዋል።
ሌላኛው አልሚ አርሶ አደር ሀሰን አልዩ፤ በሶስት ሄክታር መሬት ላይ ካለሙት ሰብል ከ400 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
በመስኖ ልማቱ ለአራት ሰዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ጠቅሰው የገበያ ትስስሩ ፈጥኖ ካልተፈጠረላቸው ለኪሳራ እዳረጋለሁ የሚል ስጋት እንዳላቸው ተናግረዋል።
በስድስት ሄክታር መሬት ላይ አትክልት እያለሙ ያሉት አርሶ አደር ማማር ሙሉጌታ፤ የተገኘው ምርት ከፍተኛ በመሆኑ የገበያ ትስስር ይፈጠርልን ሲሉ ጠይቀዋል።
በዞኑ በ2ኛው ዙር የመስኖ ልማት ከ550 ሄክታር መሬት በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን 138 ሄክታር ማልማት መቻሉ ታውቋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026