አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- በከተማ ግብርና ከራሳቸው ባለፈ ለበርካቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን በመዲናዋ በከተማ ግብርና ስራ የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከመደበኛው ግብርና በተጨማሪ በከተማ ግብርና ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በዚህም በመዲናዋ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በእንስሳትና ዶሮ እርባታ እንዲሁም በንብ ማነብ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑም ይታወቃል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማ ግብርና ላይ የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርቶቻቸውን ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።
ከሸማችነት ወደ አምራችነት በመሸጋገር የኑሮ ውድነት ጫናን ማቃለል እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠው የከተማ ግብርና ተጠቃሚው አቶ መኮንን አለሙ አንዱ ማሳያ ናቸው።
በዘርፉ የሚያገኙት ምርት ከፍጆታቸው ባለፈ ለገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም 15 ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረዋል።
ሌላው በከተማ ግብርና ተጠቃሚ የሆነው ሲሳይ አለሙ በበኩሉ በከተማ ግብርና ከተሰማራ ወዲህ ከሸማችነት መውጣቱን ገልጿል።
በዚህም ከራሱ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብም የአትክልት እና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግሯል።
የስራ እድል የተፈጠረላቸው ግለሰቦችም በሚያገኙት ገቢ ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን እየደገፉ መሆኑን ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደር እና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ የከተማ ግብርና ከዕለት ፍጆታ እስከ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል።
በመዲናዋ እስካሁን በተሰራው ስራ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በአነስተኛ ቦታ ላይ አትክልት በማልማት የምግብ ፍጆታቸውን በራሳቸው እንዲሸፍኑ እንዲሁም ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸው እንዲያድግ መደረጉን ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025