የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በከተማ ግብርና ከራሳችን ባለፈ ለበርካቶች የስራ እድል መፍጠር ችለናል - በከተማ ግብርና የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- በከተማ ግብርና ከራሳቸው ባለፈ ለበርካቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን በመዲናዋ በከተማ ግብርና ስራ የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከመደበኛው ግብርና በተጨማሪ በከተማ ግብርና ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በዚህም በመዲናዋ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በእንስሳትና ዶሮ እርባታ እንዲሁም በንብ ማነብ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑም ይታወቃል።


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማ ግብርና ላይ የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርቶቻቸውን ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

ከሸማችነት ወደ አምራችነት በመሸጋገር የኑሮ ውድነት ጫናን ማቃለል እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠው የከተማ ግብርና ተጠቃሚው አቶ መኮንን አለሙ አንዱ ማሳያ ናቸው።

በዘርፉ የሚያገኙት ምርት ከፍጆታቸው ባለፈ ለገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

በተጨማሪም 15 ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረዋል።


ሌላው በከተማ ግብርና ተጠቃሚ የሆነው ሲሳይ አለሙ በበኩሉ በከተማ ግብርና ከተሰማራ ወዲህ ከሸማችነት መውጣቱን ገልጿል።

በዚህም ከራሱ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብም የአትክልት እና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግሯል።

የስራ እድል የተፈጠረላቸው ግለሰቦችም በሚያገኙት ገቢ ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን እየደገፉ መሆኑን ገልጸዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደር እና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ የከተማ ግብርና ከዕለት ፍጆታ እስከ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል።

በመዲናዋ እስካሁን በተሰራው ስራ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በአነስተኛ ቦታ ላይ አትክልት በማልማት የምግብ ፍጆታቸውን በራሳቸው እንዲሸፍኑ እንዲሁም ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸው እንዲያድግ መደረጉን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026