የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በከተማ ግብርና ከራሳችን ባለፈ ለበርካቶች የስራ እድል መፍጠር ችለናል - በከተማ ግብርና የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- በከተማ ግብርና ከራሳቸው ባለፈ ለበርካቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን በመዲናዋ በከተማ ግብርና ስራ የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከመደበኛው ግብርና በተጨማሪ በከተማ ግብርና ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በዚህም በመዲናዋ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በእንስሳትና ዶሮ እርባታ እንዲሁም በንብ ማነብ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑም ይታወቃል።


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማ ግብርና ላይ የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርቶቻቸውን ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

ከሸማችነት ወደ አምራችነት በመሸጋገር የኑሮ ውድነት ጫናን ማቃለል እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጠው የከተማ ግብርና ተጠቃሚው አቶ መኮንን አለሙ አንዱ ማሳያ ናቸው።

በዘርፉ የሚያገኙት ምርት ከፍጆታቸው ባለፈ ለገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

በተጨማሪም 15 ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረዋል።


ሌላው በከተማ ግብርና ተጠቃሚ የሆነው ሲሳይ አለሙ በበኩሉ በከተማ ግብርና ከተሰማራ ወዲህ ከሸማችነት መውጣቱን ገልጿል።

በዚህም ከራሱ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብም የአትክልት እና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግሯል።

የስራ እድል የተፈጠረላቸው ግለሰቦችም በሚያገኙት ገቢ ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን እየደገፉ መሆኑን ገልጸዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደር እና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ የከተማ ግብርና ከዕለት ፍጆታ እስከ ኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ተናግረዋል።

በመዲናዋ እስካሁን በተሰራው ስራ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በአነስተኛ ቦታ ላይ አትክልት በማልማት የምግብ ፍጆታቸውን በራሳቸው እንዲሸፍኑ እንዲሁም ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸው እንዲያድግ መደረጉን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025