የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኮንታ ዞን በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ሴቶች ውጤታማ መሆናቸው ተገለፀ  

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አመያ፤ የካቲት 29/2017 (ኢዜአ):-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገለፁ።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሁሪያ አሊ በበኩላቸው ሴቶች በኢኮኖሚ እራሳቸውን እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል” በሚል መሪ ቃል በክልል ደረጃ በኮንታ ዞን በተለያዩ ኩነቶች እየተከበረ ነው።

በዓሉን አስመልክቶ በተዘጋጀው አውደ ርዕይና ባዛር ላይ ሴቶች የተለያዩ ምርታቸውን አቅርበዋል።


በአውደ ርዕዩ ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሁሪያ አሊ እንደገለፁት፤ ሴቶች በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ ነው።

በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ዕድሎች እየተመቻቹ እንዳሉና የተሰማሩትም ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው ይህ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስረድተዋል ።

በዚህም በዞኑ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልፀዋል።


የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ በዓሉ በሴቶች እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለመመልከት፣ የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ያሉባቸውን ችግሮች ለይቶ ለመፍታት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

በዞኑ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በከተማና በገጠር ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመው፣ የመሸጫ ቦታና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ይሰራልም ብለዋል።

በዞኑ በኤል ሀንቻኖ ወረዳ በሾታ ሻሾ ቀበሌ የሴቶች ልማት ህብረት ሰብሳቢ ወይዘሮ ጎቶሬ ጎደቶ ከ300 በላይ የሆኑ ሴቶች በመደራጀት በሰብልና በእንስሳት እርባታ ስራ ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።


በአጠቃላይ ባላቸው ስድስት ሄክታር መሬት ላይም የበጋ መስኖ ስንዴን ጨምሮ በበግ ማሞከት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቡናን ጨምሮ እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የቤተሰብን ወጪ ሸፍነው ቀሪውን ገንዘብ እየቆጠቡ ልጆቻቸውን ለማስተማር ዕድል ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በተሰጣቸው የስልጠና ድጋፍ ታግዘው የፈሳሽ ሳሙና ማምረት በመጀመራቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ወይዘሮ ትዕግስት ዶኖቾ ናቸው።

ከስድስት ወር በፊት በ60 ሺህ ብር የጀመሩት ስራ አሁን ላይ ካፒታላቸውን ከሶስት እጥፍ በላይ በማሳደግ ለሰባት ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል።


ወይዘሮ ዘይቱ ብሩ በበኩላቸው ባህላዊ ልብስ በመስራት እንደሚተዳደሩ ገልፀው ለአስር ሰዎች የስራ እድል መፍጠራቸውንና "ሴቶች ሁኔታዎችን ተቋቁመውና ወስነው ከሰሩ ውጤታማ መሆን ይችላሉ" ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026