የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኮንታ ዞን በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ሴቶች ውጤታማ መሆናቸው ተገለፀ  

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አመያ፤ የካቲት 29/2017 (ኢዜአ):-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገለፁ።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሁሪያ አሊ በበኩላቸው ሴቶች በኢኮኖሚ እራሳቸውን እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል” በሚል መሪ ቃል በክልል ደረጃ በኮንታ ዞን በተለያዩ ኩነቶች እየተከበረ ነው።

በዓሉን አስመልክቶ በተዘጋጀው አውደ ርዕይና ባዛር ላይ ሴቶች የተለያዩ ምርታቸውን አቅርበዋል።


በአውደ ርዕዩ ላይ የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሁሪያ አሊ እንደገለፁት፤ ሴቶች በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ ነው።

በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ዕድሎች እየተመቻቹ እንዳሉና የተሰማሩትም ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው ይህ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስረድተዋል ።

በዚህም በዞኑ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልፀዋል።


የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ በዓሉ በሴቶች እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለመመልከት፣ የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ያሉባቸውን ችግሮች ለይቶ ለመፍታት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

በዞኑ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በከተማና በገጠር ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመው፣ የመሸጫ ቦታና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ይሰራልም ብለዋል።

በዞኑ በኤል ሀንቻኖ ወረዳ በሾታ ሻሾ ቀበሌ የሴቶች ልማት ህብረት ሰብሳቢ ወይዘሮ ጎቶሬ ጎደቶ ከ300 በላይ የሆኑ ሴቶች በመደራጀት በሰብልና በእንስሳት እርባታ ስራ ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።


በአጠቃላይ ባላቸው ስድስት ሄክታር መሬት ላይም የበጋ መስኖ ስንዴን ጨምሮ በበግ ማሞከት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቡናን ጨምሮ እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የቤተሰብን ወጪ ሸፍነው ቀሪውን ገንዘብ እየቆጠቡ ልጆቻቸውን ለማስተማር ዕድል ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በተሰጣቸው የስልጠና ድጋፍ ታግዘው የፈሳሽ ሳሙና ማምረት በመጀመራቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ ወይዘሮ ትዕግስት ዶኖቾ ናቸው።

ከስድስት ወር በፊት በ60 ሺህ ብር የጀመሩት ስራ አሁን ላይ ካፒታላቸውን ከሶስት እጥፍ በላይ በማሳደግ ለሰባት ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል።


ወይዘሮ ዘይቱ ብሩ በበኩላቸው ባህላዊ ልብስ በመስራት እንደሚተዳደሩ ገልፀው ለአስር ሰዎች የስራ እድል መፍጠራቸውንና "ሴቶች ሁኔታዎችን ተቋቁመውና ወስነው ከሰሩ ውጤታማ መሆን ይችላሉ" ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026