
ሆሳዕና ፤የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት አገልግሎት መስጫ ህንፃዎች ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በከተሞቹ እየተካሄደ ነው፡፡
በክልሉ የክላስተር ማዕከላት በሆኑ በሆሳዕና፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ፣ ወልቂጤ፣ ቁሊቶ፣ ዱራሜና ሳጃ ከተሞች የአገልግሎት መስጫ ህንፃዎቹ ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በሆሳዕና ተገኝተው የአገልግሎት መስጫ ማዕከሉን ግንባታ በማስጀመር ላይ ይገኛሉ።
ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነቡት የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት ህንፃዎች ግንባታ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረጉም ተጠቁሟል፡፡

የቢሮዎቹ ግንባታ ለቢሮ ኪራይ የሚወጣን ወጪ በማስቀረትና ለሌላ ልማት በማዋል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም እንዲሁ፡፡
የግንባታ ስራው በሚፈለገው ጥራትና በታቀደለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ተገቢ የሆነ ክትትል እንደሚደረግም በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የግንባታ ሂደትና አፈጻጸም ክትትል በተመለከተ ሰነድ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች መሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ግንባታውን በይፋ ያስጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ እና የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የሀድያ ዞንና የሆሳዕና ከተማ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026