
ሆሳዕና ፤የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት አገልግሎት መስጫ ህንፃዎች ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በከተሞቹ እየተካሄደ ነው፡፡
በክልሉ የክላስተር ማዕከላት በሆኑ በሆሳዕና፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ፣ ወልቂጤ፣ ቁሊቶ፣ ዱራሜና ሳጃ ከተሞች የአገልግሎት መስጫ ህንፃዎቹ ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በሆሳዕና ተገኝተው የአገልግሎት መስጫ ማዕከሉን ግንባታ በማስጀመር ላይ ይገኛሉ።
ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነቡት የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት ህንፃዎች ግንባታ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረጉም ተጠቁሟል፡፡

የቢሮዎቹ ግንባታ ለቢሮ ኪራይ የሚወጣን ወጪ በማስቀረትና ለሌላ ልማት በማዋል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም እንዲሁ፡፡
የግንባታ ስራው በሚፈለገው ጥራትና በታቀደለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ተገቢ የሆነ ክትትል እንደሚደረግም በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የግንባታ ሂደትና አፈጻጸም ክትትል በተመለከተ ሰነድ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች መሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ግንባታውን በይፋ ያስጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ እና የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የሀድያ ዞንና የሆሳዕና ከተማ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026