
ሆሳዕና ፤የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት አገልግሎት መስጫ ህንፃዎች ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በከተሞቹ እየተካሄደ ነው፡፡
በክልሉ የክላስተር ማዕከላት በሆኑ በሆሳዕና፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ፣ ወልቂጤ፣ ቁሊቶ፣ ዱራሜና ሳጃ ከተሞች የአገልግሎት መስጫ ህንፃዎቹ ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በሆሳዕና ተገኝተው የአገልግሎት መስጫ ማዕከሉን ግንባታ በማስጀመር ላይ ይገኛሉ።
ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነቡት የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት ህንፃዎች ግንባታ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረጉም ተጠቁሟል፡፡

የቢሮዎቹ ግንባታ ለቢሮ ኪራይ የሚወጣን ወጪ በማስቀረትና ለሌላ ልማት በማዋል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም እንዲሁ፡፡
የግንባታ ስራው በሚፈለገው ጥራትና በታቀደለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ተገቢ የሆነ ክትትል እንደሚደረግም በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የግንባታ ሂደትና አፈጻጸም ክትትል በተመለከተ ሰነድ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች መሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ግንባታውን በይፋ ያስጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ እና የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የሀድያ ዞንና የሆሳዕና ከተማ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026