ሆሳዕና ፤የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት አገልግሎት መስጫ ህንፃዎች ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በከተሞቹ እየተካሄደ ነው፡፡
በክልሉ የክላስተር ማዕከላት በሆኑ በሆሳዕና፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ፣ ወልቂጤ፣ ቁሊቶ፣ ዱራሜና ሳጃ ከተሞች የአገልግሎት መስጫ ህንፃዎቹ ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በሆሳዕና ተገኝተው የአገልግሎት መስጫ ማዕከሉን ግንባታ በማስጀመር ላይ ይገኛሉ።
ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነቡት የሰባቱም የክላስተር ማዕከላት ህንፃዎች ግንባታ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረጉም ተጠቁሟል፡፡
የቢሮዎቹ ግንባታ ለቢሮ ኪራይ የሚወጣን ወጪ በማስቀረትና ለሌላ ልማት በማዋል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም እንዲሁ፡፡
የግንባታ ስራው በሚፈለገው ጥራትና በታቀደለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ተገቢ የሆነ ክትትል እንደሚደረግም በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የግንባታ ሂደትና አፈጻጸም ክትትል በተመለከተ ሰነድ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ርዕሰ መስተዳድሩና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች መሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ግንባታውን በይፋ ያስጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ እና የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የሀድያ ዞንና የሆሳዕና ከተማ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025