አሶሳ፤ መጋቢት 01/2017(ኢዜአ):- የአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ባህል እንዲቀየርና በሀብቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የዳቡስ ወንዝን በመጠቀም በመስኖ እያለማ ያለው ድርጅት ገለጸ።
በክልሉ ኡንዱሉ ወረዳ በእርሻና መስኖ ልማት የተሰማራው የሮኤል የተቀናጀ እርሻና መስኖ ልማት ድርጅት የዳቡስ ወንዝን በመጠቀም የመስኖ ስራ እያከናወነ መሆኑን ነው የገለጸው።
የድርጅቱ ምክትል ማናጀር አቶ ማንእንደራስ ይንገስ እንዳሉት፤ ድርጅቱ የልማት ስራውን የጀመረው ከአራት ወራት በፊት ሲሆን በአሁኑ ወቅት አስር ሄክታር ማሳ ላይ ቲማቲም፣ ሽንኩርት እና ሀባብ እያለማ ይገኛል።
እየለማ ካለው አምስት ሄክታር የቲማቲም ማሳ ላይ እስከ 7 ሺህ 500 ኩንታል ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸው፤ በቀጣይ በፍራፍሬ ምርቶች ላይ በስፋት ለመስራት የማሳ ዝግጅት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በተለይም ቤኒሻንጉል የሚታወቅበት የማንጎ ምርት ትልቁ እቅዳቸው መሆኑን አንስተዋል።
የዳቡስ ወንዝ በአካባቢው ያለው ለም አፈር ለመስኖ ልማት ስራቸው አመቺ በመሆኑ በልማቱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ተስፋ ሰንቀዋል።
ድርጅቱ በእንስሳት እና ንብ እርባታ ለመሰማራት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ 200 ፍየሎችን እንደሚያስገቡም ተናግረዋል።
የአካባቢው ማህበረሰብ የስራ ባህል እንዲቀየር እና ህብረተሰቡ ምርቱን በአቅራቢያው እንዲያኝ ማድረግ የድርጅቱ ዓላማ እንደሆነም አብራርተዋል።
ድርጅቱ 80 ለሚደርሱ ዜጎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችም የድርጅቱን የሥራ እንቅሰቃሴ እንደሚከታተሉት ምክትል ማናጀሩ አስታውቀዋል።
የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል ወጣት ገብረእግዚአብሔር ገብረእየሱስ እንደተናገረው በድርጅቱ በሚያገኘው ገቢ እራሱን እያስተዳደረ ነው።
ከዓረብ አገር ስደት መልስ በአገር ቤት የጀመረው ሥራ በመሆኑም ጥሩ አየር እየተነፈሰና እድገትን ሰንቆ በመስራት ላይ መሆኑን ተናግሯል።
ድርጅቱ በርካታ ባለሙያዎችን የያዘ መሆኑን የገለጸው ወጣቱ የተለያዩ ሙያዎችን እየተማሩ እንደሆነም ገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025