የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የወተት ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው - ግብርና ሚኒስቴር

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት የወተት ምርታማነትን ለመጨመር ከዘርፉ ተዋንያን ጋር በጋራ እየሰራ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በወተት ልማት የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በልማቱ የተሰማሩ ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት በዓለም አቀፍ እንስሳት ጥናት ኢንስቲትዩት(ILRI) ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በሚኒስቴሩ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) መንግስት የእንስሳትን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሌማት ትሩፋት ብሔራዊ ፕሮግራም ተቀርፆ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


የወተት ምርትን የሚመራ፣ በምርምር የሚደግፍ፣ የተበጣጠሱ ስራዎችን በጋራ መስራት የሚያስችል፣ ከሌሎች ሀገሮች ተሞክሮዎችን በመቅሰም በሀገር ውስጥ ተግባራዊ እንዲደረግ የሚያግዝ ቦርድ በመድረኩ እንደሚቋቋምም ጠቁመዋል።

መንግስት የወተት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዝርያ ማዳቀል፣ መኖ ማልማት፣ ወተት ማቀነባበር እና ገበያ ማስተሳሰር ላይ ያሉ ስራዎችን መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛልም ብለዋል፡፡

የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም ከመቀረፁ በፊት 5 ነጥብ 8 ቢሊየን ሊትር ወተት በዓመት ይመረት እንደነበር አስታውሰው በዘንድሮ የምርት ዘመን ከ12 ቢሊዮን ሊትር በላይ ወተት ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡


የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ(ዶ/ር) በበኩላቸው በሌማት ትሩፋት ፕሮግራም የተገኙ ስኬቶችን የተመለከተ ሰነድ አቅርበው በፕሮግራሙ የተመዘገቡ ለውጦችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።


የአለም አቀፍ እንስሳት ጥናት ኢንስቲትዩት(ILRI) ዋና ዳይሬክተር ናሙኮሎ ኮቪክ በወተት ልማት ላይ ለተሰማሩ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ መዘጋጀቱ በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

ውይይቱ እስከ ነገ እንደሚቆይ ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025