
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት የወተት ምርታማነትን ለመጨመር ከዘርፉ ተዋንያን ጋር በጋራ እየሰራ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በወተት ልማት የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በልማቱ የተሰማሩ ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት በዓለም አቀፍ እንስሳት ጥናት ኢንስቲትዩት(ILRI) ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በሚኒስቴሩ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) መንግስት የእንስሳትን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሌማት ትሩፋት ብሔራዊ ፕሮግራም ተቀርፆ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የወተት ምርትን የሚመራ፣ በምርምር የሚደግፍ፣ የተበጣጠሱ ስራዎችን በጋራ መስራት የሚያስችል፣ ከሌሎች ሀገሮች ተሞክሮዎችን በመቅሰም በሀገር ውስጥ ተግባራዊ እንዲደረግ የሚያግዝ ቦርድ በመድረኩ እንደሚቋቋምም ጠቁመዋል።
መንግስት የወተት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዝርያ ማዳቀል፣ መኖ ማልማት፣ ወተት ማቀነባበር እና ገበያ ማስተሳሰር ላይ ያሉ ስራዎችን መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛልም ብለዋል፡፡
የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም ከመቀረፁ በፊት 5 ነጥብ 8 ቢሊየን ሊትር ወተት በዓመት ይመረት እንደነበር አስታውሰው በዘንድሮ የምርት ዘመን ከ12 ቢሊዮን ሊትር በላይ ወተት ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስራት ጤራ(ዶ/ር) በበኩላቸው በሌማት ትሩፋት ፕሮግራም የተገኙ ስኬቶችን የተመለከተ ሰነድ አቅርበው በፕሮግራሙ የተመዘገቡ ለውጦችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የአለም አቀፍ እንስሳት ጥናት ኢንስቲትዩት(ILRI) ዋና ዳይሬክተር ናሙኮሎ ኮቪክ በወተት ልማት ላይ ለተሰማሩ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ መዘጋጀቱ በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
ውይይቱ እስከ ነገ እንደሚቆይ ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026