
አዲስ አበባ፤መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፦የኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎችን በማላመድ አረንጓዴ ልማትን ለመገንባት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለፁ።
በኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች ማስፈፀሚያ ረቂቅ ስትራቴጂ ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
ስትራቴጂውን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በጋራ እንዳዘጋጁት በመድረኩ ተገልጿል፡፡
በውይይቱ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ ሚኒስትር ዴኤታዎችና ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በዚሁ ወቅት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
የትራንስፖርት ዘርፉ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ለስኬታማነቱ ዘርፉን የታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነም ጠቅሰዋል።
ታዳሽ ሃይል የአየር ብክለትን ከመቀነስ ባለፈ ለነዳጅ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ለሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታ ለማዋል ያስችላል ነው ያሉት።
ከተሞችን ፅዱና ስማርት ለማድረግ የጎላ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፥ ለዚህ ደግሞ የኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎችን ማስፋፋት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ይህን ለማሳካት የሁሉንም ቅንጅት የሚጠይቅ ነው ብለዋል።
መድረኩ የኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች ማስፈፀሚያ ረቂቅ ስትራቴጂ ላይ ከመወያየት ባለፈ ወደ ተጨባጭ ስራ ለመግባት የሚያስችል መሆኑንም አስታውቀዋል።
በዚህም ታዳሽ ኃይል የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ስራ ላይ ለማዋል የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026