
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ላይ የሚያጋጥመውን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአዋሽ ባንክ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አብሮ መስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።
ለአምስት አመታት የሚቆየውን ስምምነት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጸሐይ ሽፈራው ጋር ተፈራርመዋል።
ተቋማቱ የሠራተኞች አቅምን ለመገንባት፣ የዲጂታል ኢንተርፕራይዞች እድገትን ለማፋጠንና የሥራ ፈጠራ ስልጠናን ለማበረታታት በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ማጎልበት ላይ የሚያጋጥመውን የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።

ስምምነቱ የፋይናንስ አቅርቦትን በማመቻቸትና ኢንተርፕራይዞችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ በርካታ ዜጎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ያግዛል ብለዋል።
ሚኒስቴሩ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ አስር ሚሊየን ለሚጠጉ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩን አስታውቀዋል።
ኢንተርፕራይዞቹ ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ተኪ ምርቶችን በማምረት ለሀገሪቱ ልማት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የስራ ገበያን መሰረት በማድረግ እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች ጥራት ያለው የሰው ሃይል ማፍራት መቻሉን ነው ያስረዱት።
በተቋሙ የተጀመሩ ሥራዎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጸሐይ ሽፈራው በበኩላቸው ባንኩ በዚህ ዓመት ከ4 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ለአነስተኛ እና መለስተኛ ኢንተርፕራይዞች መስጠቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም አካታች የፋይናንስ ስርዓት እንዲኖር ለአርሶና አርብቶ አደሩ ብድር እያቀረበ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026