የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ላይ የሚገጥመውን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ላይ የሚያጋጥመውን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአዋሽ ባንክ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አብሮ መስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

ለአምስት አመታት የሚቆየውን ስምምነት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጸሐይ ሽፈራው ጋር ተፈራርመዋል።

ተቋማቱ የሠራተኞች አቅምን ለመገንባት፣ የዲጂታል ኢንተርፕራይዞች እድገትን ለማፋጠንና የሥራ ፈጠራ ስልጠናን ለማበረታታት በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ማጎልበት ላይ የሚያጋጥመውን የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።


ስምምነቱ የፋይናንስ አቅርቦትን በማመቻቸትና ኢንተርፕራይዞችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ በርካታ ዜጎችን ወደ ሥራ ለማስገባት ያግዛል ብለዋል።

ሚኒስቴሩ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ አስር ሚሊየን ለሚጠጉ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩን አስታውቀዋል።

ኢንተርፕራይዞቹ ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ተኪ ምርቶችን በማምረት ለሀገሪቱ ልማት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የስራ ገበያን መሰረት በማድረግ እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች ጥራት ያለው የሰው ሃይል ማፍራት መቻሉን ነው ያስረዱት።

በተቋሙ የተጀመሩ ሥራዎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።


የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጸሐይ ሽፈራው በበኩላቸው ባንኩ በዚህ ዓመት ከ4 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ለአነስተኛ እና መለስተኛ ኢንተርፕራይዞች መስጠቱን ገልጸዋል።

በተጨማሪም አካታች የፋይናንስ ስርዓት እንዲኖር ለአርሶና አርብቶ አደሩ ብድር እያቀረበ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025