
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት በትብብር መስራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሄ አርዓያሥላሴ ናቸው።

ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) የመግባቢያ ስምምነቱ የብሔራዊ መታወቂያ(ፋይዳ) አጠቃቀምን ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ስራዎች ጋር የሚያስተሳስር መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ይህም ተቋማቱ አገልግሎትን ቀልጣፋ ግልጽና ፍትሃዊ ለማድረግ፣ የትራንስፖርት ደህንነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ሌብነትና ማጭበርበርን መከላከል የሚያስችል ስራ በተቀናጀ አግባብ ለመስራት እንደሚያስችላቸው አመልክተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026