
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት በትብብር መስራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሄ አርዓያሥላሴ ናቸው።

ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) የመግባቢያ ስምምነቱ የብሔራዊ መታወቂያ(ፋይዳ) አጠቃቀምን ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ስራዎች ጋር የሚያስተሳስር መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ይህም ተቋማቱ አገልግሎትን ቀልጣፋ ግልጽና ፍትሃዊ ለማድረግ፣ የትራንስፖርት ደህንነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ሌብነትና ማጭበርበርን መከላከል የሚያስችል ስራ በተቀናጀ አግባብ ለመስራት እንደሚያስችላቸው አመልክተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026