አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት በትብብር መስራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሄ አርዓያሥላሴ ናቸው።
ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) የመግባቢያ ስምምነቱ የብሔራዊ መታወቂያ(ፋይዳ) አጠቃቀምን ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ስራዎች ጋር የሚያስተሳስር መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ይህም ተቋማቱ አገልግሎትን ቀልጣፋ ግልጽና ፍትሃዊ ለማድረግ፣ የትራንስፖርት ደህንነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ሌብነትና ማጭበርበርን መከላከል የሚያስችል ስራ በተቀናጀ አግባብ ለመስራት እንደሚያስችላቸው አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025