የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በትግራይ ክልል ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ዝግጁ ሆነዋል

Mar 15, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤መጋቢት 5/ 2017 ( ኢዜአ)፡-በትግራይ ክልል ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ዝግጁ መሆናቸውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ።


በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራና ስልጠና ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አልጋነሽ ተሰማ (ዶ/ር)፤ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ በግብርና፣ማኑፋክቸሪንግ፣ አነስተኛ ኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ለስራ እድሉ ከተመቻቹ ፕሮጀክቶች መካከል መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።


በክልሉ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና በግል ከሚሰሩ ምሁራን ጋር በመተባበር የኢንተርፕራይዞች ፕሮጀክቶች ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑንም ተናግረዋል።


በፕሮጀክቶቹ ከ420 የሚልቁ የልማት ዘርፎችን ያቀፉ ኢንተርፕራይዞች እንደተካተቱም ኃላፊዋ ገልጸዋል።


በቀጣዮቹ ወራትም 100 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የ104 ቢዝነስ ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር የትግበራ እቅድ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል።


በፕሮጀክቱ ከተካተቱ የቢዝነስ ዓይነቶች ውስጥ የወተት እና ወተት ተዋፅኦ፣የንብ ማነብና የማር ምርት፣ የበለስና የእንጉዳይ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎችም መኖራቸውን ዘርዝረዋል።


በእውቀት ላይ የተመሰረቱ የልማት ኢንተርፕራይዞችን ማደራጀትና ተግባራዊ ማድረግ ከድህነት ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ወሳኝ በመሆኑ በሚቀጥሉት ወራት ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅት መደረጉንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026