
መቀሌ፤መጋቢት 5/ 2017 ( ኢዜአ)፡-በትግራይ ክልል ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ዝግጁ መሆናቸውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራና ስልጠና ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አልጋነሽ ተሰማ (ዶ/ር)፤ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ በግብርና፣ማኑፋክቸሪንግ፣ አነስተኛ ኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ለስራ እድሉ ከተመቻቹ ፕሮጀክቶች መካከል መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
በክልሉ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና በግል ከሚሰሩ ምሁራን ጋር በመተባበር የኢንተርፕራይዞች ፕሮጀክቶች ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑንም ተናግረዋል።
በፕሮጀክቶቹ ከ420 የሚልቁ የልማት ዘርፎችን ያቀፉ ኢንተርፕራይዞች እንደተካተቱም ኃላፊዋ ገልጸዋል።
በቀጣዮቹ ወራትም 100 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የ104 ቢዝነስ ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር የትግበራ እቅድ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱ ከተካተቱ የቢዝነስ ዓይነቶች ውስጥ የወተት እና ወተት ተዋፅኦ፣የንብ ማነብና የማር ምርት፣ የበለስና የእንጉዳይ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎችም መኖራቸውን ዘርዝረዋል።
በእውቀት ላይ የተመሰረቱ የልማት ኢንተርፕራይዞችን ማደራጀትና ተግባራዊ ማድረግ ከድህነት ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ወሳኝ በመሆኑ በሚቀጥሉት ወራት ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅት መደረጉንም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026