
መቀሌ፤መጋቢት 5/ 2017 ( ኢዜአ)፡-በትግራይ ክልል ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ዝግጁ መሆናቸውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራና ስልጠና ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አልጋነሽ ተሰማ (ዶ/ር)፤ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ በግብርና፣ማኑፋክቸሪንግ፣ አነስተኛ ኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ለስራ እድሉ ከተመቻቹ ፕሮጀክቶች መካከል መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
በክልሉ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና በግል ከሚሰሩ ምሁራን ጋር በመተባበር የኢንተርፕራይዞች ፕሮጀክቶች ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑንም ተናግረዋል።
በፕሮጀክቶቹ ከ420 የሚልቁ የልማት ዘርፎችን ያቀፉ ኢንተርፕራይዞች እንደተካተቱም ኃላፊዋ ገልጸዋል።
በቀጣዮቹ ወራትም 100 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የ104 ቢዝነስ ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር የትግበራ እቅድ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱ ከተካተቱ የቢዝነስ ዓይነቶች ውስጥ የወተት እና ወተት ተዋፅኦ፣የንብ ማነብና የማር ምርት፣ የበለስና የእንጉዳይ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎችም መኖራቸውን ዘርዝረዋል።
በእውቀት ላይ የተመሰረቱ የልማት ኢንተርፕራይዞችን ማደራጀትና ተግባራዊ ማድረግ ከድህነት ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ወሳኝ በመሆኑ በሚቀጥሉት ወራት ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅት መደረጉንም ጠቁመዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026