
መቀሌ፤መጋቢት 5/ 2017 ( ኢዜአ)፡-በትግራይ ክልል ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ዝግጁ መሆናቸውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራና ስልጠና ካቢኔ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አልጋነሽ ተሰማ (ዶ/ር)፤ለ300 ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ በግብርና፣ማኑፋክቸሪንግ፣ አነስተኛ ኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ለስራ እድሉ ከተመቻቹ ፕሮጀክቶች መካከል መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
በክልሉ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና በግል ከሚሰሩ ምሁራን ጋር በመተባበር የኢንተርፕራይዞች ፕሮጀክቶች ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑንም ተናግረዋል።
በፕሮጀክቶቹ ከ420 የሚልቁ የልማት ዘርፎችን ያቀፉ ኢንተርፕራይዞች እንደተካተቱም ኃላፊዋ ገልጸዋል።
በቀጣዮቹ ወራትም 100 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የ104 ቢዝነስ ኢንተርፕራይዞች ዝርዝር የትግበራ እቅድ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱ ከተካተቱ የቢዝነስ ዓይነቶች ውስጥ የወተት እና ወተት ተዋፅኦ፣የንብ ማነብና የማር ምርት፣ የበለስና የእንጉዳይ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎችም መኖራቸውን ዘርዝረዋል።
በእውቀት ላይ የተመሰረቱ የልማት ኢንተርፕራይዞችን ማደራጀትና ተግባራዊ ማድረግ ከድህነት ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሸጋገር ወሳኝ በመሆኑ በሚቀጥሉት ወራት ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅት መደረጉንም ጠቁመዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026