መቱ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን ቡና ከማሳ እስከ ገበያ ጥራቱን ጠብቆ እንዲቀርብ ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንዳለባቸው የዞኑ አስተዳደር አስገነዘበ።
ባለሀብቶች እና ነጋዴዎች የተሳተፉበትና በቡና ጥራትና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በመቱ ከተማ ተካሂዷል።
በዚሁ ወቅት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ እንደገለጹት የቡና ጥራትን ለማረጋገጥ ከማሳ እስከ ገበያ ድረስ እየተሰሩ በሚገኙ ሥራዎች አበረታች ውጤት እየተመዘገበ ነው።
ይሁን እንጂ አሁንም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንዳሉ ጠቁመው፣ በየዓመቱ ከዞኑ ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበው ቡና ከአጠቃላይ ዓመታዊ ምርት ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ መሆኑን በማሳያነት ጠቅሰዋል።
በመሆኑም ቡና አምራቾች፣ ነጋዴዎችና አቅራቢዎች ለቡና ጥራቱ የበኩላቸውን ድርሻ ከመወጣት ባሻገር ሕገ-ወጥ የቡና ንግድን ጨምሮ በጥራት ላይ ችግር የሚያስከትሉ ነገሮችን በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል።
የቡና ገበያ ከዓለም አቀፍ ነባራዊና ተለዋዋጭ ሁኔታ ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ነጋዴዎችም ቡናን በተገቢው ጊዜ ለገበያ ማቅረባቸው ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግና እንደሀገር የሚጠበቀውን ጥቅም ማግኘት የሚያስችል መሆኑም ከግንዛቤ ማስገባት አለባቸው ነው ያሉት።
በቡና ልማት ዘርፍ ያለው የኢንቨስትመንት ሁኔታም ትኩረት የሚሻ በመሆኑ ባለሀብቶች ከመንግስት ጋር በቅርበት እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ጥራቱ የተረጋገጠ ቡና ለገበያ ለማቅረብ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ብዙ እንደሚጠበቅና የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል አቶ ዴሬሳ ተሰማ፣ ሕገ-ወጥ የቡና ንግድን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ደካማ መሆን ለቡና ጥራት ችግር መንስኤ እንደሆነ አንስተዋል።
በመስኩ ለሚሰማሩ አካላት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የሚደርገው ጥረት መጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል።
የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰጠው ትኩረት ለጥራቱም መሰጠት እንዳለበት ያነሱት ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ፈቀደ ማሞ ናቸው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025