የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢሉአባቦር ዞን ቡና ከማሳ ጀምሮ እስከ ገበያ ጥራቱን ለማስጠበቅ ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት ይገባቸዋል - የዞኑ አስተዳደር

Mar 15, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን ቡና ከማሳ እስከ ገበያ ጥራቱን ጠብቆ እንዲቀርብ ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንዳለባቸው የዞኑ አስተዳደር አስገነዘበ።


ባለሀብቶች እና ነጋዴዎች የተሳተፉበትና በቡና ጥራትና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በመቱ ከተማ ተካሂዷል።


በዚሁ ወቅት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ እንደገለጹት የቡና ጥራትን ለማረጋገጥ ከማሳ እስከ ገበያ ድረስ እየተሰሩ በሚገኙ ሥራዎች አበረታች ውጤት እየተመዘገበ ነው።


ይሁን እንጂ አሁንም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንዳሉ ጠቁመው፣ በየዓመቱ ከዞኑ ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበው ቡና ከአጠቃላይ ዓመታዊ ምርት ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ መሆኑን በማሳያነት ጠቅሰዋል።


በመሆኑም ቡና አምራቾች፣ ነጋዴዎችና አቅራቢዎች ለቡና ጥራቱ የበኩላቸውን ድርሻ ከመወጣት ባሻገር ሕገ-ወጥ የቡና ንግድን ጨምሮ በጥራት ላይ ችግር የሚያስከትሉ ነገሮችን በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል።


የቡና ገበያ ከዓለም አቀፍ ነባራዊና ተለዋዋጭ ሁኔታ ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ነጋዴዎችም ቡናን በተገቢው ጊዜ ለገበያ ማቅረባቸው ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግና እንደሀገር የሚጠበቀውን ጥቅም ማግኘት የሚያስችል መሆኑም ከግንዛቤ ማስገባት አለባቸው ነው ያሉት።


በቡና ልማት ዘርፍ ያለው የኢንቨስትመንት ሁኔታም ትኩረት የሚሻ በመሆኑ ባለሀብቶች ከመንግስት ጋር በቅርበት እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።


የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ጥራቱ የተረጋገጠ ቡና ለገበያ ለማቅረብ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ብዙ እንደሚጠበቅና የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።


ከተሳታፊዎቹ መካከል አቶ ዴሬሳ ተሰማ፣ ሕገ-ወጥ የቡና ንግድን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ደካማ መሆን ለቡና ጥራት ችግር መንስኤ እንደሆነ አንስተዋል።


በመስኩ ለሚሰማሩ አካላት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የሚደርገው ጥረት መጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል።


የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰጠው ትኩረት ለጥራቱም መሰጠት እንዳለበት ያነሱት ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ፈቀደ ማሞ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026