
መቱ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በኢሉአባቦር ዞን ቡና ከማሳ እስከ ገበያ ጥራቱን ጠብቆ እንዲቀርብ ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንዳለባቸው የዞኑ አስተዳደር አስገነዘበ።
ባለሀብቶች እና ነጋዴዎች የተሳተፉበትና በቡና ጥራትና ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በመቱ ከተማ ተካሂዷል።
በዚሁ ወቅት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ እንደገለጹት የቡና ጥራትን ለማረጋገጥ ከማሳ እስከ ገበያ ድረስ እየተሰሩ በሚገኙ ሥራዎች አበረታች ውጤት እየተመዘገበ ነው።
ይሁን እንጂ አሁንም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንዳሉ ጠቁመው፣ በየዓመቱ ከዞኑ ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበው ቡና ከአጠቃላይ ዓመታዊ ምርት ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ መሆኑን በማሳያነት ጠቅሰዋል።
በመሆኑም ቡና አምራቾች፣ ነጋዴዎችና አቅራቢዎች ለቡና ጥራቱ የበኩላቸውን ድርሻ ከመወጣት ባሻገር ሕገ-ወጥ የቡና ንግድን ጨምሮ በጥራት ላይ ችግር የሚያስከትሉ ነገሮችን በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል።

የቡና ገበያ ከዓለም አቀፍ ነባራዊና ተለዋዋጭ ሁኔታ ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ነጋዴዎችም ቡናን በተገቢው ጊዜ ለገበያ ማቅረባቸው ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግና እንደሀገር የሚጠበቀውን ጥቅም ማግኘት የሚያስችል መሆኑም ከግንዛቤ ማስገባት አለባቸው ነው ያሉት።
በቡና ልማት ዘርፍ ያለው የኢንቨስትመንት ሁኔታም ትኩረት የሚሻ በመሆኑ ባለሀብቶች ከመንግስት ጋር በቅርበት እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ጥራቱ የተረጋገጠ ቡና ለገበያ ለማቅረብ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ብዙ እንደሚጠበቅና የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል አቶ ዴሬሳ ተሰማ፣ ሕገ-ወጥ የቡና ንግድን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ደካማ መሆን ለቡና ጥራት ችግር መንስኤ እንደሆነ አንስተዋል።
በመስኩ ለሚሰማሩ አካላት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የሚደርገው ጥረት መጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል።
የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰጠው ትኩረት ለጥራቱም መሰጠት እንዳለበት ያነሱት ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ፈቀደ ማሞ ናቸው።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026