ገንዳ ውሃ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- ዩኒዬኖችንና የሕብረት ሥራ ማህበራትን በማጠናከር በገበያ ማረጋጋት ሥራ የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ገልጸ።
መተማ የገበሬዎች ሁለገብ ዩኒዬን ከ8 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ያቀረባቸውን መሰረታዊ ሸቀጦች ዛሬ ለሸማች ህብረት ሥራ ማህበራት አከፋፍሏል።
የምዕራብ ጎንደር ዞን ህብረት ሥራ ማህበራት ተጠሪ ጽህፈት ኃላፊ ወይዘሮ በልጣ ጌትነት በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በዞኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጉዳት ለመቀነስ እየተሰራ ነው።
ዩኒዬኖችንና የህብረት ሥራ ማህበራትን በማጠናከር የግብርናና የፋብሪካ የፍጆታ ምርቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ለዚህም በወረዳና በከተሞች ለሸማች ሕብረት ሥራ ማህበራት ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ ተዘዋዋሪ ብድር ለመስጠት ታቅዶ ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ጥቅም ላይ መዋሉን ነው የገለጹት።
ከ2ሺህ ኩንታል በላይ ማሽላ፣ ከ500 ኩንታል በላይ ጤፍ፣ ከ10 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት፣ ከ800 ኩንታል በላይ ስኳርና ሌሎች ምርቶች ለሸማቹ መከፋፈላቸውን አስረድተዋል።
የመተማ ገበሬዎች ሁለገብ ዩኒዮን ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብቴ ዘውዱ በበኩላቸው፣ ዛሬ ለሸማች ህብረት ሥራ ማህበራት የተከፋፈሉት ከ8 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 10ሺህ ሊትር ዘይት፣ 100 ኩንታል የዳቦ ዱቄት እና 469 ኩንታል ስኳር ናቸው።
ዩኒየኑ በገበያ ማረጋጋት ተግባር የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልፀው፣ ከ6ሺህ ኩንታል በላይ የግብርና ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑንም ተናግረዋል።
ይህን ተግባሩን በቀጣይም አጠናክሮ ለማስቀጠል ያቀረቡት 40 ሚሊዮን ብር ብድር መፈቀዱንም አመልክተዋል
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በበኩላቸው ሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ባላቸው ሀብት የፍጆታ እቃዎችን በማስመጣት ለህብረተሰቡ ማከፋፈል እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የሸማች ህብረት ሥራ ማህበራት እያከናወኑት ያለው ገበያን የማረጋጋት ሥራ ያለአግባብ ለመክበር የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ ስግብግብ ነጋዴዎችን እንቅስቃሴ ይገታል ብለዋል።
የዞኑ አስተዳደር ገበያው እንዲረጋጋ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከሚሰራው ሥራ በተጨማሪ የህብረት ሥራ ማህበራትን የመደገፍ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በምዕራብ ጎንደር ዞን 119 ሕብረት ሥራ ማህበራት እና ሁለት ዩኒየኖች እንዳሉ ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025