የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ ዩኒዬኖችንና የሕብረት ሥራ ማህበራትን በማጠናከር በገበያ ማረጋጋት ሥራ የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተደረገ ነው

Mar 15, 2025

IDOPRESS

ገንዳ ውሃ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- ዩኒዬኖችንና የሕብረት ሥራ ማህበራትን በማጠናከር በገበያ ማረጋጋት ሥራ የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ገልጸ።

መተማ የገበሬዎች ሁለገብ ዩኒዬን ከ8 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ያቀረባቸውን መሰረታዊ ሸቀጦች ዛሬ ለሸማች ህብረት ሥራ ማህበራት አከፋፍሏል።


የምዕራብ ጎንደር ዞን ህብረት ሥራ ማህበራት ተጠሪ ጽህፈት ኃላፊ ወይዘሮ በልጣ ጌትነት በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በዞኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጉዳት ለመቀነስ እየተሰራ ነው።

ዩኒዬኖችንና የህብረት ሥራ ማህበራትን በማጠናከር የግብርናና የፋብሪካ የፍጆታ ምርቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።


ለዚህም በወረዳና በከተሞች ለሸማች ሕብረት ሥራ ማህበራት ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ ተዘዋዋሪ ብድር ለመስጠት ታቅዶ ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ጥቅም ላይ መዋሉን ነው የገለጹት።

ከ2ሺህ ኩንታል በላይ ማሽላ፣ ከ500 ኩንታል በላይ ጤፍ፣ ከ10 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት፣ ከ800 ኩንታል በላይ ስኳርና ሌሎች ምርቶች ለሸማቹ መከፋፈላቸውን አስረድተዋል።


የመተማ ገበሬዎች ሁለገብ ዩኒዮን ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብቴ ዘውዱ በበኩላቸው፣ ዛሬ ለሸማች ህብረት ሥራ ማህበራት የተከፋፈሉት ከ8 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 10ሺህ ሊትር ዘይት፣ 100 ኩንታል የዳቦ ዱቄት እና 469 ኩንታል ስኳር ናቸው።

ዩኒየኑ በገበያ ማረጋጋት ተግባር የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልፀው፣ ከ6ሺህ ኩንታል በላይ የግብርና ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑንም ተናግረዋል።

ይህን ተግባሩን በቀጣይም አጠናክሮ ለማስቀጠል ያቀረቡት 40 ሚሊዮን ብር ብድር መፈቀዱንም አመልክተዋል


የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በበኩላቸው ሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ባላቸው ሀብት የፍጆታ እቃዎችን በማስመጣት ለህብረተሰቡ ማከፋፈል እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የሸማች ህብረት ሥራ ማህበራት እያከናወኑት ያለው ገበያን የማረጋጋት ሥራ ያለአግባብ ለመክበር የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ ስግብግብ ነጋዴዎችን እንቅስቃሴ ይገታል ብለዋል።

የዞኑ አስተዳደር ገበያው እንዲረጋጋ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከሚሰራው ሥራ በተጨማሪ የህብረት ሥራ ማህበራትን የመደገፍ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን 119 ሕብረት ሥራ ማህበራት እና ሁለት ዩኒየኖች እንዳሉ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026