
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ከተማ 154ሺህ 923 ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ፕሮግራም በይፋ ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ጃንጥራር አባይ ፕሮግራሙን በከተማ ደረጃ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የከተማ ልማት ሴፍትኔት ፕሮግራሙ ለሶስተኛ ዙር በከተማው እንደሚካሄድ ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት በተካሄዱ ሁለት ዙር የልማት ሴፍትኔት ፕሮግራሞች ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
ዛሬ በተጀመረው ሶስተኛ ዙር የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ላይ የሚሳተፋ ነዋሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ በፕሮግራሙ 154ሺህ 923 ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተመላክቷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026