
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ከተማ 154ሺህ 923 ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ፕሮግራም በይፋ ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ጃንጥራር አባይ ፕሮግራሙን በከተማ ደረጃ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የከተማ ልማት ሴፍትኔት ፕሮግራሙ ለሶስተኛ ዙር በከተማው እንደሚካሄድ ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት በተካሄዱ ሁለት ዙር የልማት ሴፍትኔት ፕሮግራሞች ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
ዛሬ በተጀመረው ሶስተኛ ዙር የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ላይ የሚሳተፋ ነዋሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ በፕሮግራሙ 154ሺህ 923 ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተመላክቷል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026