
ሚዛን አማን፣መጋቢት 7/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።
በሠላምና ልማት ዙሪያ የሚያተኩር የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።
ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳደሩ እንዳመለከቱት፥ ባለፉት ሦስት ዓመታት ተኩል በክልሉ የሠላም ግንባታ፣የልማትና፣የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ሲከናወኑ ቆየተዋል።
በዚህም ውጤት መገኘቱን ገልጸው፥በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ከፀጥታ ጋር ተያይዞ የነበረው ችግር እየተፈታ ለልማት ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።
ይህን አጠናክሮ በማስቀጠልና ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልል በተለይ የዞኑን ሠላም በማስጠበቅ ልማትን ለማጠናከር በሚቻልበት ላይ ዛሬ እየመከረ ያለው መድረክ በተመሳሳይ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።
በአማን ከተማ እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የክልሉና የምዕራብ ኦሞ ዞን አመራር አባላት እንዲሁም ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026