
ሚዛን አማን፣መጋቢት 7/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።
በሠላምና ልማት ዙሪያ የሚያተኩር የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።
ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳደሩ እንዳመለከቱት፥ ባለፉት ሦስት ዓመታት ተኩል በክልሉ የሠላም ግንባታ፣የልማትና፣የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ሲከናወኑ ቆየተዋል።
በዚህም ውጤት መገኘቱን ገልጸው፥በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ከፀጥታ ጋር ተያይዞ የነበረው ችግር እየተፈታ ለልማት ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።
ይህን አጠናክሮ በማስቀጠልና ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልል በተለይ የዞኑን ሠላም በማስጠበቅ ልማትን ለማጠናከር በሚቻልበት ላይ ዛሬ እየመከረ ያለው መድረክ በተመሳሳይ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።
በአማን ከተማ እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የክልሉና የምዕራብ ኦሞ ዞን አመራር አባላት እንዲሁም ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026