ሚዛን አማን፣መጋቢት 7/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።
በሠላምና ልማት ዙሪያ የሚያተኩር የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።
ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳደሩ እንዳመለከቱት፥ ባለፉት ሦስት ዓመታት ተኩል በክልሉ የሠላም ግንባታ፣የልማትና፣የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ሲከናወኑ ቆየተዋል።
በዚህም ውጤት መገኘቱን ገልጸው፥በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ከፀጥታ ጋር ተያይዞ የነበረው ችግር እየተፈታ ለልማት ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።
ይህን አጠናክሮ በማስቀጠልና ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልል በተለይ የዞኑን ሠላም በማስጠበቅ ልማትን ለማጠናከር በሚቻልበት ላይ ዛሬ እየመከረ ያለው መድረክ በተመሳሳይ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።
በአማን ከተማ እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የክልሉና የምዕራብ ኦሞ ዞን አመራር አባላት እንዲሁም ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025