የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የፈጠራ አቅም ያላቸው ታዳጊዎች ለማፍራት አዳዲስ መርሐ ግብሮች ወደ ተግባር ገብተዋል

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፦ ዕምቅ የፈጠራ አቅምና ችሎታ ያላቸው ታዳጊዎችን ለማፍራት አዳዲስ መርሐ ግብሮች ወደ ተግባር መግባታቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ገለፀ።

ሚኒስቴሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር "ብሩህ እናት" የተሰኘ የሴት ኢኖቬተሮች የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የቡት ካምፕ ስልጠና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።


የስራና ክህሎት ሚንስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በወቅቱ እንዳሉት የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት የቴክኖሎጂ ሽግግር ማድረግ አስፈላጊ ነው።

ለዚህም የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዳዲስ ቴክኖሎጂ የሚያመነጩና የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች የሚደግፉ መርሐ ግብሮችን እየቀረጸ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ይህንንም ተከትሎ አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ እምቅ አቅምና ችሎታ ያላቸውን ታዳጊዎችና ወጣቶች ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች ሃሳባቸው ወደ ተግባር ተቀይሮ ተጨባጭ ውጤት እንዲያስገኝ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ረገድ አዳዲስ ቴክኖሎጂ የሚያመነጩና የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች የሚደግፉ ፕሮግራሞች በመቅረፅ ተግባራዊ እየተደረጉ ነው ብለዋል፡፡

“ማሰልጠን፣ መሸለም እና ማብቃት” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው “ብሩህ ኢትዮጵያ” ሀገር አቀፍ የቢዝነስ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ከእነዚህ ፕሮግራሞች መካከል አንዱ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ በውድድር ያለፉ 50 የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ሴቶች ተጨማሪ ስልጠና እንደሚወስዱ ጠቅሰዋል።

ከስልጠና በኋላ በውድድሩ ለሚያሸንፉ 10 ምርጦች ከመቶ ሺህ እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ሽልማት እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026