የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በበልግ ወቅት ከ520 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰበሎች ይለማል - የክልሉ ግብርና በሮ

Mar 19, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበልግ ወቅት ከ520 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን ታቅዶ ዝግጅት እየደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ሃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ520 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ ነው።


በዚህም በቆሎ፣ ማሽላ፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ሌሎች የሆርቲካልቸር ሰብሎችን በማልማት ከ52 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ በሁሉም ወቅቶች የግብርና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በሚደረጉ ጥረቶች አርሶ አደሩ በማሳው የሚያሳልፈው ጊዜ እየጨመረና ለውጥ እየታየ መምጣቱንም ተናግረዋል።

በቅድመ በልግ ያሉትን ጊዜያቶች እርጥበትና ያሉ የውሃ አማራጮች በመጠቀም ልማቱን ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በክልሉ በልግን ጨምሮ ለ2017/2018 የምርት ዘመን ጥቅም ላይ የሚውል ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል በለይ የአፈር ማዳበሪያ እየቀረበ ነውም ብለዋል።

አርሶ አደሩ በልማቱ ውጤታማ እንዲሆን ከምርጥ ዘር አቅርቦት በተጨማሪ የተቀናጀ ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።


በክልሉ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊና የእርሻ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሁሴን ሙስጠፋ በበኩላቸው በወረዳው በበልግ ከ4 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ነው።

በአሁኑ ወቅትም የመሬት ዝግጅት፣ የግብአት አቅርቦትና የባለሙያ ድጋፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።


በክልሉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ነዋሪ አርሶ አደር ኢብራሒም ረዲ እና አርሶ አደር ሰለሞን አስራት በበኩላቸው ለበልግ እርሻ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዶቦና ጎላ ቀበሌ በሦስት ሄክታር መሬት ላይ በበጋ መስኖ ካለሙት አትክልትና ስንዴ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው በአሁኑ ወቅትም መሬቱን ለበልግ እርሻ እያዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ለበልግ አርሻ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየቀረባቸው መሆኑን ገልጸው፣ በልማቱ የግብርና ባለሙያን ድጋፍ ተጠቅመው ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን አመልክተዋል።


ከበጋ መስኖ ልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት አርሶ አደር ሰለሞን አስራት በበኩላቸው፣ በበልግ እርሻው ውጤታማ ለመሆን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በበልግ እርሻ በሦስት ሄክታር መሬት ላይ በቆሎ ለማልማት የእርሻ ስራና መሰል ዘግጅቶችን እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025