የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መከፋፈሉ ተገለጸ

Mar 19, 2025

IDOPRESS

መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መከፋፈሉን የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ገለጸ።

ኤጀንሲው የ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ግብይት ላይ ያተኮረ መግለጫ ሰጥቷል።

የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ሀላፊ አቶ ጀማል ከድር በሰጡት መግለጫ በክልሉ ዘንድሮ ከ11 ነጥብ 4 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማደበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ታቅዷል ብለዋል።

ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 2 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታል በላይ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

በእስካሁኑ ሂደትም ለክልሉ ከሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያ ከ4 ሚሊዬን ኩንታል በላይ የሚሆነው ወደ አገር ውስጥ መግባቱን ገልጸዋል።

የሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያ ለበጋ መስኖ፣ ለበልግና ለመኸር አዝመራ የሚውል ሲሆን እስካሁን ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተከፋፍሏል ብለዋል።

የአፈር ማዳበሪያው የወቅቱን የዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ ገበያ ሁኔታዎች ታሳቢ ያደረገ ተጨማሪ ድጎማ ተደርጎ ለአርሶ አደሩ እየቀረበ መሆኑን አስረድተዋል።

ለዚሁ እንዲያግዝ ዘንድሮ 32 ቢሊየን ብር የክልሉ መንግስት ለአፈር ማዳበሪያ ግዢ ድጎማ ማድረጉንም አስረድተዋል።

የአፈር ማዳበሪያ ግብይትም በዲጂታል ዘዴ ታግዞ የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው አርሶ አደሩም ባለው የእርሻ መሬት መጠን ብቻ ማደበሪያ እንዲያገኝ ይደረጋል ብለዋል።

የክልሉ አርሶ አደሮችም ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ለምርት ዘመኑ የሚያስፈልጋቸውን የአፈር ማዳበሪያ በጊዜ እንዲገዙ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026