
መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መከፋፈሉን የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ገለጸ።
ኤጀንሲው የ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ግብይት ላይ ያተኮረ መግለጫ ሰጥቷል።
የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ሀላፊ አቶ ጀማል ከድር በሰጡት መግለጫ በክልሉ ዘንድሮ ከ11 ነጥብ 4 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማደበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ታቅዷል ብለዋል።
ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 2 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታል በላይ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም ለክልሉ ከሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያ ከ4 ሚሊዬን ኩንታል በላይ የሚሆነው ወደ አገር ውስጥ መግባቱን ገልጸዋል።
የሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያ ለበጋ መስኖ፣ ለበልግና ለመኸር አዝመራ የሚውል ሲሆን እስካሁን ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተከፋፍሏል ብለዋል።
የአፈር ማዳበሪያው የወቅቱን የዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ ገበያ ሁኔታዎች ታሳቢ ያደረገ ተጨማሪ ድጎማ ተደርጎ ለአርሶ አደሩ እየቀረበ መሆኑን አስረድተዋል።
ለዚሁ እንዲያግዝ ዘንድሮ 32 ቢሊየን ብር የክልሉ መንግስት ለአፈር ማዳበሪያ ግዢ ድጎማ ማድረጉንም አስረድተዋል።
የአፈር ማዳበሪያ ግብይትም በዲጂታል ዘዴ ታግዞ የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው አርሶ አደሩም ባለው የእርሻ መሬት መጠን ብቻ ማደበሪያ እንዲያገኝ ይደረጋል ብለዋል።
የክልሉ አርሶ አደሮችም ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ለምርት ዘመኑ የሚያስፈልጋቸውን የአፈር ማዳበሪያ በጊዜ እንዲገዙ አሳስበዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026