
መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መከፋፈሉን የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ገለጸ።
ኤጀንሲው የ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ግብይት ላይ ያተኮረ መግለጫ ሰጥቷል።
የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ሀላፊ አቶ ጀማል ከድር በሰጡት መግለጫ በክልሉ ዘንድሮ ከ11 ነጥብ 4 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማደበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ታቅዷል ብለዋል።
ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 2 ነጥብ 3 ሚሊየን ኩንታል በላይ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም ለክልሉ ከሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያ ከ4 ሚሊዬን ኩንታል በላይ የሚሆነው ወደ አገር ውስጥ መግባቱን ገልጸዋል።
የሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያ ለበጋ መስኖ፣ ለበልግና ለመኸር አዝመራ የሚውል ሲሆን እስካሁን ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተከፋፍሏል ብለዋል።
የአፈር ማዳበሪያው የወቅቱን የዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ ገበያ ሁኔታዎች ታሳቢ ያደረገ ተጨማሪ ድጎማ ተደርጎ ለአርሶ አደሩ እየቀረበ መሆኑን አስረድተዋል።
ለዚሁ እንዲያግዝ ዘንድሮ 32 ቢሊየን ብር የክልሉ መንግስት ለአፈር ማዳበሪያ ግዢ ድጎማ ማድረጉንም አስረድተዋል።
የአፈር ማዳበሪያ ግብይትም በዲጂታል ዘዴ ታግዞ የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው አርሶ አደሩም ባለው የእርሻ መሬት መጠን ብቻ ማደበሪያ እንዲያገኝ ይደረጋል ብለዋል።
የክልሉ አርሶ አደሮችም ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ለምርት ዘመኑ የሚያስፈልጋቸውን የአፈር ማዳበሪያ በጊዜ እንዲገዙ አሳስበዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026