
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- በሌማት ትሩፋት ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
የሌማት ትሩፋት ስራዎችን በተመለከተ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ እጅግ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ገልጸዋል።
አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የተጀመሩ የሌማት ትሩፋት ስራዎች አበረታች መሆናቸውን አንስተዋል።
በእንቁላል፣ በወተት፣ በስጋ ምርት ኢትዮጵያ ቀድማ የጀመረችው እንቅስቃሴ ትክክለኛ መሆኑ አሁን ላይ ያለው የአለም የገበያ ቀውስ ጥሩ አመላካች ሊሆን ይችላል ብለዋል።
የተሰራው ስራ በቂ ነው ብለን አናምንም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እስካሁን በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ እመርታ መመዝገቡን ጠቁመዋል።
በቀጣይም እነዚህን ስራዎች አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026