
ደሴ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ) ፦አገልግሎቱ የቴክኖሎጂ ምዝገባ ስርዓቱን በማስፋት በዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማስተካከል በሚቻልበት ላይ በኮምቦልቻ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በምክክር መድረኩ የአገልግሎቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ሞላ ትዕዛዙ እንደገለጹት ፤ በክልሉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ተደራሽ በማድረግ መስሪያ ቤታቸውን የመረጃ ቋት ምንጭ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
በዚህም በክልሉ በሚገኙ 122 ማዕከላት የተጀመረው የቴክኖሎጂ ምዝገባ አሰራር በቅልጥፍና እና ጥራት ባለው የመረጃ ቅብብሎሽ ውጤት ማምጣት መቻሉን ተናግረዋል።
የቴክኖሎጂ ምዝገባው ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹና ቀርፋፋ አሰራሮችንና የቅንጀት ክፍተቶችን በማስተካከል በኩል አበረታች ለውጥ አምጥቷል ብለዋል።
ከኢትዮ ቴሌኮም እና ሌሎችም ተቋማት ጋር በመተባበር ወደ ተለያዩ ማዕከላት ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለማስፋት በተደረገ ጥረት ዘንድሮ በ166 ጤና ተቋማት የሞትና ልደት ኩነት ምዝገባ መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም ባለፉት ስምንት ወራት ከ378 ሺህ በላይ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ መካሄዱን ያመለከቱት አቶ ሞላ በቀሪ ወራት ቴክኖሎጂውን በማስፋት ምዝገባውን በንቅናቄ ለማቀላጠፍ መድረኩ አስፈልጓል ብለዋል።
በደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ወሳኝ ኩነቶች የምዝገባ ቡድን መሪ አቶ ጌታቸው መሀመድ በበኩላቸው፥ በሁሉም ማዕከላት በቴክኖሎጂው የተደገፈ ምዝገባ በመጀመራቸው ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡
በዚህም ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን አስረድተዋል።
በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ጽህፈት ቤት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ቡድን መሪ አቶ መንግስቴ ወልደየስ ፤ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ምዝገባን ለማስጀመር ግብዓት የማሟላት ሥራ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡
በዚህ መድረክ መሳተፋቸውም ቀደም ሲል ከጀመሩ ዞኖችና ወረዳዎች ልምድ መቅሰማቸው ቴክኖሎጂውን ለመተግበር ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይም የክልል፣ የተለያዩ ዞኖችና የከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ አመራር አባላትና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026