ደሴ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ) ፦አገልግሎቱ የቴክኖሎጂ ምዝገባ ስርዓቱን በማስፋት በዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማስተካከል በሚቻልበት ላይ በኮምቦልቻ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በምክክር መድረኩ የአገልግሎቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ሞላ ትዕዛዙ እንደገለጹት ፤ በክልሉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ተደራሽ በማድረግ መስሪያ ቤታቸውን የመረጃ ቋት ምንጭ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
በዚህም በክልሉ በሚገኙ 122 ማዕከላት የተጀመረው የቴክኖሎጂ ምዝገባ አሰራር በቅልጥፍና እና ጥራት ባለው የመረጃ ቅብብሎሽ ውጤት ማምጣት መቻሉን ተናግረዋል።
የቴክኖሎጂ ምዝገባው ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹና ቀርፋፋ አሰራሮችንና የቅንጀት ክፍተቶችን በማስተካከል በኩል አበረታች ለውጥ አምጥቷል ብለዋል።
ከኢትዮ ቴሌኮም እና ሌሎችም ተቋማት ጋር በመተባበር ወደ ተለያዩ ማዕከላት ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለማስፋት በተደረገ ጥረት ዘንድሮ በ166 ጤና ተቋማት የሞትና ልደት ኩነት ምዝገባ መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም ባለፉት ስምንት ወራት ከ378 ሺህ በላይ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ መካሄዱን ያመለከቱት አቶ ሞላ በቀሪ ወራት ቴክኖሎጂውን በማስፋት ምዝገባውን በንቅናቄ ለማቀላጠፍ መድረኩ አስፈልጓል ብለዋል።
በደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ወሳኝ ኩነቶች የምዝገባ ቡድን መሪ አቶ ጌታቸው መሀመድ በበኩላቸው፥ በሁሉም ማዕከላት በቴክኖሎጂው የተደገፈ ምዝገባ በመጀመራቸው ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡
በዚህም ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን አስረድተዋል።
በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ጽህፈት ቤት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ቡድን መሪ አቶ መንግስቴ ወልደየስ ፤ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ምዝገባን ለማስጀመር ግብዓት የማሟላት ሥራ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡
በዚህ መድረክ መሳተፋቸውም ቀደም ሲል ከጀመሩ ዞኖችና ወረዳዎች ልምድ መቅሰማቸው ቴክኖሎጂውን ለመተግበር ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይም የክልል፣ የተለያዩ ዞኖችና የከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ አመራር አባላትና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025