የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ በቴክኖሎጂ አሰራር በመታገዝ የማስፋፋት ትግባር እየተከናወነ ነው

Apr 3, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ) ፦አገልግሎቱ የቴክኖሎጂ ምዝገባ ስርዓቱን በማስፋት በዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማስተካከል በሚቻልበት ላይ በኮምቦልቻ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።


በምክክር መድረኩ የአገልግሎቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ሞላ ትዕዛዙ እንደገለጹት ፤ በክልሉ የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ተደራሽ በማድረግ መስሪያ ቤታቸውን የመረጃ ቋት ምንጭ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡


በዚህም በክልሉ በሚገኙ 122 ማዕከላት የተጀመረው የቴክኖሎጂ ምዝገባ አሰራር በቅልጥፍና እና ጥራት ባለው የመረጃ ቅብብሎሽ ውጤት ማምጣት መቻሉን ተናግረዋል።


የቴክኖሎጂ ምዝገባው ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹና ቀርፋፋ አሰራሮችንና የቅንጀት ክፍተቶችን በማስተካከል በኩል አበረታች ለውጥ አምጥቷል ብለዋል።


ከኢትዮ ቴሌኮም እና ሌሎችም ተቋማት ጋር በመተባበር ወደ ተለያዩ ማዕከላት ለማስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


በተጨማሪም የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለማስፋት በተደረገ ጥረት ዘንድሮ በ166 ጤና ተቋማት የሞትና ልደት ኩነት ምዝገባ መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡


በዚህም ባለፉት ስምንት ወራት ከ378 ሺህ በላይ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ መካሄዱን ያመለከቱት አቶ ሞላ በቀሪ ወራት ቴክኖሎጂውን በማስፋት ምዝገባውን በንቅናቄ ለማቀላጠፍ መድረኩ አስፈልጓል ብለዋል።


በደሴ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ወሳኝ ኩነቶች የምዝገባ ቡድን መሪ አቶ ጌታቸው መሀመድ በበኩላቸው፥ በሁሉም ማዕከላት በቴክኖሎጂው የተደገፈ ምዝገባ በመጀመራቸው ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡


በዚህም ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን አስረድተዋል።


በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ጽህፈት ቤት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ቡድን መሪ አቶ መንግስቴ ወልደየስ ፤ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ምዝገባን ለማስጀመር ግብዓት የማሟላት ሥራ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡


በዚህ መድረክ መሳተፋቸውም ቀደም ሲል ከጀመሩ ዞኖችና ወረዳዎች ልምድ መቅሰማቸው ቴክኖሎጂውን ለመተግበር ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።


በመድረኩ ላይም የክልል፣ የተለያዩ ዞኖችና የከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ አመራር አባላትና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026