
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ-ቴሌኮም ከመልቲ ቾይዝ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ዲ ኤስ ቲቪ ስትሪም ጥቅል የተባለ አገልግሎት ይፋ አድርጓል።
ስምምነቱ ቀልጣፋ ፈጣንና በየትኛውም ጊዜና ቦታ የላቀ ጥራት ያላቸውን ይዘቶች በተለያዩ ስማርት ስልኮች ማግኘት የሚያስችል ነው።
ጥቅሉ ከድምጽና ኢንተርኔት ግንኙነት በተጨማሪ የተለያዩ ተወዳጅ የስፖርት ቻናሎችን ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ማየት የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል፡፡

እንዲሁም ሀገርኛ ይዘቶችን፣ ዓለም አቀፍ ፊልሞችን፣ ዶክመንተሪዎችንና የተለያዩ ሾዎችን መመልከት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚህ ወቅት ትብብሩ ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉንም አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተጓዘበት ያለውን ርቀት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የመልቲ ቾይስ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ገሊላ ገብረሚካኤል በበኩላቸው ዲኤስቲቪ ስትሪም ጥቅል አገልግሎት የተለያዩ አማራጮችን የያዘ ጎጆ ቤተሰብ፣ ሜዳ ፕላስና ፕሪሚየምን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም ደንበኞች የሚፈልጉትን አገልግሎት መርጠው እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026