
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ-ቴሌኮም ከመልቲ ቾይዝ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ዲ ኤስ ቲቪ ስትሪም ጥቅል የተባለ አገልግሎት ይፋ አድርጓል።
ስምምነቱ ቀልጣፋ ፈጣንና በየትኛውም ጊዜና ቦታ የላቀ ጥራት ያላቸውን ይዘቶች በተለያዩ ስማርት ስልኮች ማግኘት የሚያስችል ነው።
ጥቅሉ ከድምጽና ኢንተርኔት ግንኙነት በተጨማሪ የተለያዩ ተወዳጅ የስፖርት ቻናሎችን ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ማየት የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል፡፡

እንዲሁም ሀገርኛ ይዘቶችን፣ ዓለም አቀፍ ፊልሞችን፣ ዶክመንተሪዎችንና የተለያዩ ሾዎችን መመልከት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚህ ወቅት ትብብሩ ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉንም አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተጓዘበት ያለውን ርቀት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የመልቲ ቾይስ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ገሊላ ገብረሚካኤል በበኩላቸው ዲኤስቲቪ ስትሪም ጥቅል አገልግሎት የተለያዩ አማራጮችን የያዘ ጎጆ ቤተሰብ፣ ሜዳ ፕላስና ፕሪሚየምን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም ደንበኞች የሚፈልጉትን አገልግሎት መርጠው እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026