አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያ ግብርና በታሪክ ትልቅ ድል ያስመዘገበበት መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።
የግብርና ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኖች ባለፉት 7 ዓመታት በለውጡ መንግስት በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ስኬቶች ላይ ‘ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና!’ በሚል መሪ ሀሳብ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የሚኒስቴሩ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፈ ሚኒስትር ዴኤታ እያሱ ኤልያስ (ፕ/ር) ባለፉት ሰባት የለውጥ አመታት እንደ ሀገር በርካታ ውጤቶችና ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል
ከለውጡ በፊት በኢትዮጵያ ላይ የተጋረጠውን የመበታተን አደጋና ስጋት ተቀርፎ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር የተደረገበት ቀን እንደነበር አውስተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘውም በለውጥ ዓመታቱ የኢትዮጵያ ግብርና በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ትልቅ ድል የተመዘገበበት ነው ብለዋል።
በስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ አሻራና በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮች የተመዘገቡ ውጤቶች የምግብ ዋስትናን እና ስርዓተ ምግብ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ግብርና ለመገንባት በሚደረገው ጥረት መሰረት የተጣለበት እንደሆነ አመልክተዋል።
የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት የለውጡ አመታት በኢኮኖሚው ዘርፍ በግብርና ላይ ብቻ የተንጠለጠለውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ብዝሃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ለማድረግ ከግብርናው ባለፈ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝምና በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ዘርፎች ላይ ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል።
በግብርናው ዘርፍ የመጣው ለውጥ የሚታወስና ብዙ የታሪክ እጥፋቶች የመጣበት መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸው የተገኘውን ድል ለማጽናትና ለማስቀጠል አመራሩና ሰራተኛው በበለጠ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው አሳስበዋል።
በለውጡ ዓመታት የተገኙ ድሎችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም አጠቃላይ በኢኮኖሚውና በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን የሚዳስስ ሰነድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት እንደተደረገበት የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025