
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያ ግብርና በታሪክ ትልቅ ድል ያስመዘገበበት መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።
የግብርና ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኖች ባለፉት 7 ዓመታት በለውጡ መንግስት በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ስኬቶች ላይ ‘ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና!’ በሚል መሪ ሀሳብ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የሚኒስቴሩ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፈ ሚኒስትር ዴኤታ እያሱ ኤልያስ (ፕ/ር) ባለፉት ሰባት የለውጥ አመታት እንደ ሀገር በርካታ ውጤቶችና ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል
ከለውጡ በፊት በኢትዮጵያ ላይ የተጋረጠውን የመበታተን አደጋና ስጋት ተቀርፎ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር የተደረገበት ቀን እንደነበር አውስተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘውም በለውጥ ዓመታቱ የኢትዮጵያ ግብርና በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ትልቅ ድል የተመዘገበበት ነው ብለዋል።
በስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ አሻራና በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቮች የተመዘገቡ ውጤቶች የምግብ ዋስትናን እና ስርዓተ ምግብ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ግብርና ለመገንባት በሚደረገው ጥረት መሰረት የተጣለበት እንደሆነ አመልክተዋል።
የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት የለውጡ አመታት በኢኮኖሚው ዘርፍ በግብርና ላይ ብቻ የተንጠለጠለውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ብዝሃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ለማድረግ ከግብርናው ባለፈ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝምና በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ዘርፎች ላይ ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል።
በግብርናው ዘርፍ የመጣው ለውጥ የሚታወስና ብዙ የታሪክ እጥፋቶች የመጣበት መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸው የተገኘውን ድል ለማጽናትና ለማስቀጠል አመራሩና ሰራተኛው በበለጠ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው አሳስበዋል።
በለውጡ ዓመታት የተገኙ ድሎችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም አጠቃላይ በኢኮኖሚውና በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን የሚዳስስ ሰነድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት እንደተደረገበት የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026