አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2017(ኢዜአ)፡- የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ በዲጂታል ማንነት ባሳዩት የአመራርነት ሚና ኦክታ ከተሰኘ የአሜሪካ ኩባንያ ዓለም አቀፍ እውቅና አግኝተዋል።
ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ሳን ፍራንሲስኮ ያደረገው ኩባንያ አቶ ዮዳሔን በዓለም ደረጃ በዲጂታል ማንነት የአመራርነት ሚና ካላቸው 25 ሰዎች አንዱ በሚል እውቅና ሰጥቷቸዋል።
በብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም መርሃ ግብር 12 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን መመዝገባቸውንና ይህን ቁጥር እ.አ.አ በ2025 ላይ 45 ሚሊዮን ለማድረስ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ ኩባንያው ገልጿል።
አጠቃላይ 90 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በፋይዳ መታወቂያ ተደራሽ የማድረግ እቅድም ተይዟል።
የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ የዲጂታል ማንነት ሁሉም ቦታ ተደራሽ የመሆን፣ የዜጎችን ኑሮ የመቀየር እና አካታችነትን የማረጋገጥ ሰፊ አቅም እንዳለውም አመልክተዋል።
የፕሮግራሙ ግብ ዜጎችን መመዝገብ ብቻ አይደለም የሚሉት አቶ ዮዳሔ በመታወቂያው ዜጎች እያገኙ ያለው አገልግሎት ስራችን ከሌላው የተለየ ያደርገዋል ሲሉም ተናግረዋል።
ለማህበረሰቡ እና ተቋማት ግንዛቤ መፍጠርን ጨምሮ ሌሎች የነበሩ ፈተናዎችን በማለፍ በፕሮግራሙ አስገራሚ ለውጦች መገኘታቸውን አመልክተዋል።
የፋይዳ የቴክኖሎጂ እና ህጋዊ ማዕቀፍ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስተሳሰር የተከናወነው ስራ ትልቅ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
ፕሮግራሙ የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እንደሆነም ጨምረው ገልጸዋል።
ኦክታ እ.አአ በ2009 የተቋቋመ በዲጂታል ማንነት እና መረጃ አስተዳደር ላይ የሚሰራ የአሜሪካ ኩባንያ ነው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025