
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 25/2017(ኢዜአ)፡- የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ በዲጂታል ማንነት ባሳዩት የአመራርነት ሚና ኦክታ ከተሰኘ የአሜሪካ ኩባንያ ዓለም አቀፍ እውቅና አግኝተዋል።
ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ሳን ፍራንሲስኮ ያደረገው ኩባንያ አቶ ዮዳሔን በዓለም ደረጃ በዲጂታል ማንነት የአመራርነት ሚና ካላቸው 25 ሰዎች አንዱ በሚል እውቅና ሰጥቷቸዋል።
በብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም መርሃ ግብር 12 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን መመዝገባቸውንና ይህን ቁጥር እ.አ.አ በ2025 ላይ 45 ሚሊዮን ለማድረስ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ ኩባንያው ገልጿል።
አጠቃላይ 90 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በፋይዳ መታወቂያ ተደራሽ የማድረግ እቅድም ተይዟል።

የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ የዲጂታል ማንነት ሁሉም ቦታ ተደራሽ የመሆን፣ የዜጎችን ኑሮ የመቀየር እና አካታችነትን የማረጋገጥ ሰፊ አቅም እንዳለውም አመልክተዋል።
የፕሮግራሙ ግብ ዜጎችን መመዝገብ ብቻ አይደለም የሚሉት አቶ ዮዳሔ በመታወቂያው ዜጎች እያገኙ ያለው አገልግሎት ስራችን ከሌላው የተለየ ያደርገዋል ሲሉም ተናግረዋል።
ለማህበረሰቡ እና ተቋማት ግንዛቤ መፍጠርን ጨምሮ ሌሎች የነበሩ ፈተናዎችን በማለፍ በፕሮግራሙ አስገራሚ ለውጦች መገኘታቸውን አመልክተዋል።
የፋይዳ የቴክኖሎጂ እና ህጋዊ ማዕቀፍ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስተሳሰር የተከናወነው ስራ ትልቅ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
ፕሮግራሙ የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እንደሆነም ጨምረው ገልጸዋል።
ኦክታ እ.አአ በ2009 የተቋቋመ በዲጂታል ማንነት እና መረጃ አስተዳደር ላይ የሚሰራ የአሜሪካ ኩባንያ ነው።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026