ደሴ፤ መጋቢት 28/2017(ኢዜአ)፡- የ'ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ' የኢንቨስትመንት ጥያቄያቸው ፈጣን ምላሽ እንዲያገኝ ማስቻሉን ኢዜአ ያነጋገራቸው የደሴ ከተማ ባለሃብቶች ገለጹ።
“ኢትዮጵያ ታምርት፣ እኛም እንሸምት“ በሚል መሪ ሀሳብ የደሴ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡
ከመድረኩ ተሳታፊ ባለሀብቶች መካከል ወይዘሮ የውብዳር ሞላ እንዳሉት፤ የሚስማር ፋብሪካ ለመገንባት ቦታ ባለማግኘታቸው ተቸግረው ቆይተዋል፡፡
በ'ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ' በመጀመሩ ግን ከሁለት ሺህ 800 ካሬ ሜትር በላይ መሬት በማግኘታቸው በ105 ሚሊዮን ብር ካፒታል በአጭር ጊዜ ግንባታውን አጠናቀው ወደ ምርት ሥራ ገብተዋል።
ለ58 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።
በሞልና አፓርታማ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ አህመድ ኑር ስጦታው በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ችግሮቻችን መፈታት በመቻላችን ፈጥነን ወደ ሥራ መግባት ችለናል ብለዋል፡፡
ከከተማ አስተዳደሩ 500 ካሬ ሜትር መሬት ተቀብለው በአንድ ቢሊዮን ብር ካፒታል ወደ ግንባታ መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡
የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት ለኢንቨስትመንት ዘርፉ በተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት መመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡
ቀጣይም በዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስተካከል በስፋት ተኪ ምርት እንዲመረትና ገበያው መረጋጋት እንዲችል በቅንጅት እንሰራለን ሲሉ ገልጸዋል።
ንቅናቄው በዘርፉ ችግሮች በመፍታት ኢንቨስትመንትን ማነቃቃት መቻሉን የደሴ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለባቸው ሰይድ ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ስምንት የኢንዱስትሪ ፋብሪካዎች ምርት መግባታቸውን ጠቁመው፤ 36 ፋብሪካዎች ደግሞ በግንባታ ላይ ናቸው ብለዋል።
በጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ26 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 125 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ እንዳወጡ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025