የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በ'ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ' የኢንቨስትመንት ጥያቄያችን ተመልሷል

Apr 7, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ መጋቢት 28/2017(ኢዜአ)፡- የ'ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ' የኢንቨስትመንት ጥያቄያቸው ፈጣን ምላሽ እንዲያገኝ ማስቻሉን ኢዜአ ያነጋገራቸው የደሴ ከተማ ባለሃብቶች ገለጹ።

“ኢትዮጵያ ታምርት፣ እኛም እንሸምት“ በሚል መሪ ሀሳብ የደሴ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡

ከመድረኩ ተሳታፊ ባለሀብቶች መካከል ወይዘሮ የውብዳር ሞላ እንዳሉት፤ የሚስማር ፋብሪካ ለመገንባት ቦታ ባለማግኘታቸው ተቸግረው ቆይተዋል፡፡

በ'ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ' በመጀመሩ ግን ከሁለት ሺህ 800 ካሬ ሜትር በላይ መሬት በማግኘታቸው በ105 ሚሊዮን ብር ካፒታል በአጭር ጊዜ ግንባታውን አጠናቀው ወደ ምርት ሥራ ገብተዋል።

ለ58 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።


በሞልና አፓርታማ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩት አቶ አህመድ ኑር ስጦታው በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ችግሮቻችን መፈታት በመቻላችን ፈጥነን ወደ ሥራ መግባት ችለናል ብለዋል፡፡

ከከተማ አስተዳደሩ 500 ካሬ ሜትር መሬት ተቀብለው በአንድ ቢሊዮን ብር ካፒታል ወደ ግንባታ መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡

የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በበኩላቸው፤ ባለፉት ዓመታት ለኢንቨስትመንት ዘርፉ በተሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት መመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡

ቀጣይም በዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስተካከል በስፋት ተኪ ምርት እንዲመረትና ገበያው መረጋጋት እንዲችል በቅንጅት እንሰራለን ሲሉ ገልጸዋል።

ንቅናቄው በዘርፉ ችግሮች በመፍታት ኢንቨስትመንትን ማነቃቃት መቻሉን የደሴ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለባቸው ሰይድ ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ስምንት የኢንዱስትሪ ፋብሪካዎች ምርት መግባታቸውን ጠቁመው፤ 36 ፋብሪካዎች ደግሞ በግንባታ ላይ ናቸው ብለዋል።

በጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ26 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 125 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ እንዳወጡ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026