
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ የቤልት እና ሮድ ኢኒሼቲቭ ለኢትዮጵያ እና ቻይና አጋርነት መጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ገለጹ።
አምባሳደር ተፈራ ከቻይና ዴይሊ ዕለታዊ ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ የኢትዮጵያ እና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከጀመረ 55 ዓመታትን ማስቆጠሩን አውስተዋል።
ለሁለቱ ሀገራት ጠንካራ እና የጠለቀ አጋርነት የቤልት እና ሮድ ኢኒሼቲቭ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል።
ቻይና ወደብን ጨምሮ ያሏት የንግድ አማራጮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያም ያለውን እድል በመጠቀም በቻይና የኤሌክትሮኒክስ ንግድ የበይነ መረብ አማራጭ ብሔራዊ የንግድ ቋት በመክፈት የግብርና ምርት ኤክስፖርቷን እያሳደገች እንደምትገኝ አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ቡና በቻይና በተለይም በወጣቱ ትውልድ ይበልጥ ተወዳጅነቱ እየጨመረ መምጣቱን ነው አምባሳደሩ የገለጹት።

ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልከው የቡና መጠን እና አጠቃላይ የሀገራቱ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ በከፍተኛ ሁኔታ አድጓል።
ኢትዮጵያ የቻይና ዋንጫ የንግድ አጋር ስትሆን ቻይናም ለኢትዮጵያ ቁልፍ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ሸሪክ ናት ብለዋል።
አምባሳደር ተፈራ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ልውውጥ ለማደጉ የቤልት እና ሮድ ኢኒሼቲቭ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል ነው ያሉት።
የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት የኢኒሼቲቩ አካል እንደሆነና የንግድ ትስስርን እያሳላጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያ ወደ ቻይና ለምትልከው የቡና መጠን ማደግ ወሳኝ አበርክቶ እንዳለውም ነው ያስረዱት።
ቻይና የኢትዮጵያን የኢነርጂ ዘርፍ እየደገፈች እንደምትገኝና የገናሌ ዳዋ ሁለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ እና የአዳማ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ለአብነት ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት ላይ በትኩረት እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸው የኤሌክትሪክ መኪና ገበያን የዚሁ ስራ አካል መሆኑን አንስተዋል።
አምስት አስርት ዓመታትን የተሻገረው የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ጠንካራ የንግድ እና ትብብር ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው ብለዋል።
ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁት የትራንስፖርት እና የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያን በማዘመን በኩል ድርሻቸው ወሳኝ እንደሆነም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1970 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026