
ደሴ፣መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፡ -እየጣለ ያለው ዝናብ ለበልግ አብቃይ አካባቢዎች ምቹ በመሆኑ አርሶ አደሩ የሰብል ልማቱን ማቀላጠፍ እንዳለበት በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምስራቅ አማራ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አሳሰበ፡፡
የማዕከሉ የልማት ሚቲዎሮሎጂ ዴስክ ኃላፊ አቶ እንዳላማው ወልዴ ለኢዜአ እንደገለጹት የዘንድሮው የበልግ ዝናብ ፈጥነው ለሚደርሱ ሰብሎች ምቹ ነው።
አርሶ አደሩ በምስራቅ አማራ ዞኖች የሚዘንበውን ቀላልና መካከለኛ ዝናብ ተጠቅሞ ፈጥነው መድረስ የሚችሉ ሰብሎች ላይ በማተኮር የዘር ስራውን ማቀላጠፍ እንዳለበት ገልጸዋል።
ከዚህ ጎን ለጎንም የሚዘንበውን ዝናብ በማሳ ዳር ዳር አቅቦ በማስቀረትና ወደ ግድቦችና ኩሬዎች በማስገባት የዘሩት ሰብል ምርታማ እንዲሆን አልመው መስራት እንደለባቸው አሳስበዋል።
የበልግ ዝናቡ ለሰብል ልማት፣ ለእንሰሳት ግጦሽ፣ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማትም የሚያስገኘው ጠቀሜታ ከፍ ያለ በመሆኑ በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
የበልግ ዝናቡ ደረቅና ሞቃት የአየር ጸባይ ስለሚፈጥር ህብረተሰቡ ከተለያዩ በሽታዎች እራሱን እንዲጠብቅ ያሳሰቡት አቶ እንዳላማው በተለይ የወባ መራቢያ ሥፍራዎችን ማጽዳት ይኖርበታል ብለዋል፡፡
የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ በበኩላቸው በዞኑ የበልግ ዝናብን በመጠቀም ከ50 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በተለያየ የሰብል ዘር ተሸፍኗል ብለዋል፡፡
አርሶ አደሩ ያገኘውን እርጥበት ተጠቅሞ ወደ ልማቱ እንዲገባ በየደረጃው ባሉ የግብርና ባለሙያዎች እገዛ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
በዞኑ ከ104 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበልግ በማልማት ከሁለት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከዞኑ ግብርና መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026