
አሶሳ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 56 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገብቶ ስርጭት መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የግብርና ግብዓት አቅርቦት እና የምርት ግብይት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ በቀለ ለኢዜአ እንደገለፁት በምርት ዘመኑ ለክልሉ 231ሺህ 340 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ተመድቧል።

ከዚህ ውስጥም በእስካሁኑ በተደረገ የማጓጓዝ ስራ በአሶሳ እና መተከል ዞን በሚገኙ ማዕከላት 56ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገብቶ ስርጭት መጀመሩን ገልፀዋል።
አምስት ሺህ ኩንታሉ ደግሞ ለአርሶ አደሩ መሠራጨቱን ዳይሬክተሩ አክለዋል።
የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ መድረስ አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅት ከመግባቱ በፊት ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ እና ክረምት ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ምቹ ባልሆኑ አካባቢዎች በጊዜ እንዲደርስ መልካም አጋጣሚ መሆኑንም ተናግረዋል።
የክልሉ መንግስት የግብርና ግብዓት መመሪያ በማዘጋጀት አርሶ አደሩ ማዳበሪያን ያለምንም እንግልት እንዲያገኝ እየተደረገ እንደሆነም ገልፀዋል።
በዚህም አርሶ አደሩ በማሳው ልክ የአፈር ማዳበሪያ እንዲያገኝ እና ከሶስተኛ ወገን ነፃ በሆነ መልኩ እንዲወስድ የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት።
በአሁኑ ወቅት አርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ እንዲወስድ የንቅናቄ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፤ አርሶ አደሩ የእርሻ ወቅት ከመድረሱ በፊት የማዳበሪያ ግዥ በመፈጸም ለእርሻ ማሳቸው ዝግጁ እንዲያደርጉ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።
በክልሉ ከአፈር ማዳበሪያ በተጨማሪ የምርጥ ዘር አቅርቦት መኖሩን ተናግረው፥ ከተደለደለው 5ሺህ 292 ኩንታል ውስጥ 800 ኩንታል ገብቶ ስርጭት መጀመሩን ጠቅሰዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026