የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 56 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገብቷል

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 56 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገብቶ ስርጭት መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የግብርና ግብዓት አቅርቦት እና የምርት ግብይት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ በቀለ ለኢዜአ እንደገለፁት በምርት ዘመኑ ለክልሉ 231ሺህ 340 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ተመድቧል።


ከዚህ ውስጥም በእስካሁኑ በተደረገ የማጓጓዝ ስራ በአሶሳ እና መተከል ዞን በሚገኙ ማዕከላት 56ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገብቶ ስርጭት መጀመሩን ገልፀዋል።

አምስት ሺህ ኩንታሉ ደግሞ ለአርሶ አደሩ መሠራጨቱን ዳይሬክተሩ አክለዋል።


የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ መድረስ አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅት ከመግባቱ በፊት ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ እና ክረምት ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ምቹ ባልሆኑ አካባቢዎች በጊዜ እንዲደርስ መልካም አጋጣሚ መሆኑንም ተናግረዋል።


የክልሉ መንግስት የግብርና ግብዓት መመሪያ በማዘጋጀት አርሶ አደሩ ማዳበሪያን ያለምንም እንግልት እንዲያገኝ እየተደረገ እንደሆነም ገልፀዋል።


በዚህም አርሶ አደሩ በማሳው ልክ የአፈር ማዳበሪያ እንዲያገኝ እና ከሶስተኛ ወገን ነፃ በሆነ መልኩ እንዲወስድ የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት።


በአሁኑ ወቅት አርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ እንዲወስድ የንቅናቄ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፤ አርሶ አደሩ የእርሻ ወቅት ከመድረሱ በፊት የማዳበሪያ ግዥ በመፈጸም ለእርሻ ማሳቸው ዝግጁ እንዲያደርጉ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።


በክልሉ ከአፈር ማዳበሪያ በተጨማሪ የምርጥ ዘር አቅርቦት መኖሩን ተናግረው፥ ከተደለደለው 5ሺህ 292 ኩንታል ውስጥ 800 ኩንታል ገብቶ ስርጭት መጀመሩን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026