
አሶሳ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 56 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገብቶ ስርጭት መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የግብርና ግብዓት አቅርቦት እና የምርት ግብይት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ በቀለ ለኢዜአ እንደገለፁት በምርት ዘመኑ ለክልሉ 231ሺህ 340 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ተመድቧል።

ከዚህ ውስጥም በእስካሁኑ በተደረገ የማጓጓዝ ስራ በአሶሳ እና መተከል ዞን በሚገኙ ማዕከላት 56ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገብቶ ስርጭት መጀመሩን ገልፀዋል።
አምስት ሺህ ኩንታሉ ደግሞ ለአርሶ አደሩ መሠራጨቱን ዳይሬክተሩ አክለዋል።
የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ መድረስ አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅት ከመግባቱ በፊት ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ እና ክረምት ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ምቹ ባልሆኑ አካባቢዎች በጊዜ እንዲደርስ መልካም አጋጣሚ መሆኑንም ተናግረዋል።
የክልሉ መንግስት የግብርና ግብዓት መመሪያ በማዘጋጀት አርሶ አደሩ ማዳበሪያን ያለምንም እንግልት እንዲያገኝ እየተደረገ እንደሆነም ገልፀዋል።
በዚህም አርሶ አደሩ በማሳው ልክ የአፈር ማዳበሪያ እንዲያገኝ እና ከሶስተኛ ወገን ነፃ በሆነ መልኩ እንዲወስድ የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት።
በአሁኑ ወቅት አርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ እንዲወስድ የንቅናቄ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፤ አርሶ አደሩ የእርሻ ወቅት ከመድረሱ በፊት የማዳበሪያ ግዥ በመፈጸም ለእርሻ ማሳቸው ዝግጁ እንዲያደርጉ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።
በክልሉ ከአፈር ማዳበሪያ በተጨማሪ የምርጥ ዘር አቅርቦት መኖሩን ተናግረው፥ ከተደለደለው 5ሺህ 292 ኩንታል ውስጥ 800 ኩንታል ገብቶ ስርጭት መጀመሩን ጠቅሰዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026