የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የማዕድን ልማት አሰራሮችን በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እያደገ ነው

Apr 9, 2025

IDOPRESS

መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የማዕድን ልማት አሰራሮችን በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እያደገ መምጣቱን የክልሉ ማዕድን ልማት ባለስልጣን ገለጸ።

ከክልሉ በበጀት ዓመቱ ባለፉት ወራት የተለያየ የማዕድናትን በብሔራዊ ባንክ በኩል ለውጪ ገበያ በማቅረብ 605 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።

በተጨማሪም ለአገር ውስጥ ገበያ ከቀረበ የማዕድን ምርት ከ1 ቢሊየን 600 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ባለሥልጣኑ አስታውቋል።

የኦሮሚያ ክልል ማዕድን ልማት ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ለሜሳ ለኢዜአ እንደተናገሩት ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ የክልሉ መንግስት ለማዕድን ዘርፍ በሰጠው ትኩረት ከዘርፉ ትልቅ ጥቅም እየተገኘ ነው።

በዚህም የማዕድን ዘርፉ በአግባቡ እንዲመራ ለማድረግ ደንቦች፣ ህጎችና መመሪያዎች ተዘጋጅተው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

በተደረጉ ማሻሻያዎች ከማዕድን ሀብቱ ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን ገልጸው ከዘርፉ የሚገኘው ገቢም እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት ለሀገር ውስጥ ገበያ ከቀረበው የማዕድን ምርት 2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እስከ አሁን 1 ቢሊየን 600 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን ነው የገለጹት።

በክልሉ የማዕድን ልማት ዘርፍ የውጭ ምንዛሪ ከማስገኘት ባለፈ ለበርካታ ዜጎችም የስራ እድል እየፈጠረ መምጣቱንም አስረድተዋል።


በባለስልጣኑ የጂኦሎጂ ባለሙያ የሆኑት አቶ አለማየሁ ኦልጂራ በበኩላቸው በክልሉ የተለያዩ ማዕድናት የሚገኙበትን ቦታ ለመለየት ብዙ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት በክልሉ እስከ አሁን ለኢንዱስትሪ ግብዓት፤ ለጌጣጌጥ እና ብረታብረት ምርት የሚውሉ 76 አይነት ማዕድናት መለየታቸውን ገልጸዋል።

ከእነዚህ ውስጥ ብዙዎቹን ወደ ምርት በማስገባት ለኢንዱስትሪ ግብዓት እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026