
ዲላ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፡-በዲላ ከተማ አስተዳደር ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጀመረ።
በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የከተማው ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ምንተስኖት ከበደ እንደገለጹት የመሰረተ ልማት መስፋፊያዎቹ ለህዝብ የልማት ጥያቄ ቅድሚያ የሰጡ ናቸው።

በማስፋፊያ ግንባታው ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ መንገድና የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦ፣ ሁለት መለስተኛ ድልድዮችና አንድ ማዕከልን ጨምሮ 25 ፕሮጀክቶች መካተታቸውን አመልክተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ለ3 ሺህ 456 ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የከተማዋን ደረጃ የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ግንባታው በቀጣይ ሦስት ወራት እንደሚጠናቀቅ የገለጹት አቶ ምንተስኖት፣ ለሥራው የሚያስፈልገው ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ወጪ በዞኑና በከተማ አስተዳደሩ እንደሚሸፈንም ተናግረዋል።
የዲላ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን የብዙ ጊዜ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተወካይ አቶ መንግሥቱ ተክሌ ናቸው።

ዛሬ ግንባታቸው የተጀመሩት የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የእዚሁ አካል መሆናቸውን ያስረዱት ሃላፊው፣ የልማት ሥራዎቹ የከተማውን ገጽታና ደረጃ ከማሳደግ ባለፈ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።
ህብረተሰቡ ለልማት ሥራዎቹ ስኬታማነት በተለያየ መንገድ ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ለተሰሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ሊያደርግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሳለኝ ኮርሜ በበኩላቸው ለዓመታት ሲያነሱት የነበረው የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ እያገኘ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀው፣ የግንባታ ሥራው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026