ዲላ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፡-በዲላ ከተማ አስተዳደር ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጀመረ።
በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የከተማው ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ምንተስኖት ከበደ እንደገለጹት የመሰረተ ልማት መስፋፊያዎቹ ለህዝብ የልማት ጥያቄ ቅድሚያ የሰጡ ናቸው።
በማስፋፊያ ግንባታው ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ መንገድና የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦ፣ ሁለት መለስተኛ ድልድዮችና አንድ ማዕከልን ጨምሮ 25 ፕሮጀክቶች መካተታቸውን አመልክተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ለ3 ሺህ 456 ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የከተማዋን ደረጃ የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ግንባታው በቀጣይ ሦስት ወራት እንደሚጠናቀቅ የገለጹት አቶ ምንተስኖት፣ ለሥራው የሚያስፈልገው ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ወጪ በዞኑና በከተማ አስተዳደሩ እንደሚሸፈንም ተናግረዋል።
የዲላ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን የብዙ ጊዜ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተወካይ አቶ መንግሥቱ ተክሌ ናቸው።
ዛሬ ግንባታቸው የተጀመሩት የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የእዚሁ አካል መሆናቸውን ያስረዱት ሃላፊው፣ የልማት ሥራዎቹ የከተማውን ገጽታና ደረጃ ከማሳደግ ባለፈ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።
ህብረተሰቡ ለልማት ሥራዎቹ ስኬታማነት በተለያየ መንገድ ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ለተሰሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ሊያደርግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሳለኝ ኮርሜ በበኩላቸው ለዓመታት ሲያነሱት የነበረው የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ እያገኘ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀው፣ የግንባታ ሥራው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025