
ዲላ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፡-በዲላ ከተማ አስተዳደር ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጀመረ።
በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የከተማው ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ምንተስኖት ከበደ እንደገለጹት የመሰረተ ልማት መስፋፊያዎቹ ለህዝብ የልማት ጥያቄ ቅድሚያ የሰጡ ናቸው።

በማስፋፊያ ግንባታው ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ መንገድና የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦ፣ ሁለት መለስተኛ ድልድዮችና አንድ ማዕከልን ጨምሮ 25 ፕሮጀክቶች መካተታቸውን አመልክተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ለ3 ሺህ 456 ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የከተማዋን ደረጃ የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ግንባታው በቀጣይ ሦስት ወራት እንደሚጠናቀቅ የገለጹት አቶ ምንተስኖት፣ ለሥራው የሚያስፈልገው ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ወጪ በዞኑና በከተማ አስተዳደሩ እንደሚሸፈንም ተናግረዋል።
የዲላ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን የብዙ ጊዜ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተወካይ አቶ መንግሥቱ ተክሌ ናቸው።

ዛሬ ግንባታቸው የተጀመሩት የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የእዚሁ አካል መሆናቸውን ያስረዱት ሃላፊው፣ የልማት ሥራዎቹ የከተማውን ገጽታና ደረጃ ከማሳደግ ባለፈ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።
ህብረተሰቡ ለልማት ሥራዎቹ ስኬታማነት በተለያየ መንገድ ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ለተሰሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ሊያደርግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሳለኝ ኮርሜ በበኩላቸው ለዓመታት ሲያነሱት የነበረው የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ እያገኘ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀው፣ የግንባታ ሥራው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026