የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዲላ ከተማ ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጀመረ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፡-በዲላ ከተማ አስተዳደር ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጀመረ።

በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የከተማው ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ምንተስኖት ከበደ እንደገለጹት የመሰረተ ልማት መስፋፊያዎቹ ለህዝብ የልማት ጥያቄ ቅድሚያ የሰጡ ናቸው።


በማስፋፊያ ግንባታው ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ መንገድና የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦ፣ ሁለት መለስተኛ ድልድዮችና አንድ ማዕከልን ጨምሮ 25 ፕሮጀክቶች መካተታቸውን አመልክተዋል።

ፕሮጀክቶቹ ለ3 ሺህ 456 ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የከተማዋን ደረጃ የሚያሳድጉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

ግንባታው በቀጣይ ሦስት ወራት እንደሚጠናቀቅ የገለጹት አቶ ምንተስኖት፣ ለሥራው የሚያስፈልገው ከ91 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ወጪ በዞኑና በከተማ አስተዳደሩ እንደሚሸፈንም ተናግረዋል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን የብዙ ጊዜ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተወካይ አቶ መንግሥቱ ተክሌ ናቸው።


ዛሬ ግንባታቸው የተጀመሩት የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የእዚሁ አካል መሆናቸውን ያስረዱት ሃላፊው፣ የልማት ሥራዎቹ የከተማውን ገጽታና ደረጃ ከማሳደግ ባለፈ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።

ህብረተሰቡ ለልማት ሥራዎቹ ስኬታማነት በተለያየ መንገድ ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ለተሰሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ሊያደርግ እንደሚገባም አሳስበዋል።


ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሳለኝ ኮርሜ በበኩላቸው ለዓመታት ሲያነሱት የነበረው የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ እያገኘ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀው፣ የግንባታ ሥራው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025