
ጋምቤላ፤መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የግብርናውን ልማት በሜካናይዜሽን በመደገፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
በዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ "መርሲ ኮርፕስ"/Mercy Corps/ በተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅትና በጋምቤላ ብድርና ቁጠባ ተቋም ትብብር የተገዙ ዘጠኝ የእርሻ ትራክተሮች ለክልሉ ድጋፍ ተደርጓል።
ርዕሰ መስተዳደሯ በርክክቡ ላይ እንዳሉት፥ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋትና ልማቱን በማሳለጥ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተግተን እንሰራለን።
በተለይም በመጪው የመኸር እርሻ አንድም መሬት ጾም እንዳያድር የግብርና ልማቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
ርዕሰ መስተዳድሯ ለዓለም ምግብ ፕሮግራም፣መርሲ ኮርፕስ ለተሰኘ ግብር ሰናይ ድርጅት፣ ለክልሉ ብድርና ቁጠባ ተቋምና ለአኝዋሃ ልማት ማህበር ዘርፉን ለማገዝ ላደረጉት ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።
ምክትል ርዕሰ መስተደድሩ ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) በበኩላቸው፥በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመንና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የአጋር አካላት ድጋፋና ትብብር ወሳኝ ነው።
የክልሉ መንግስት ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመላቀቅ ሰፊ ጥረት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በዓለም ምግብ ፕሮግራም፣መርሲ ኮርፕስ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርድት እና ከክልሉ ብድርና ቁጠባ ተቋም ጋር በመተባበር የክልሉን የግብርና ልማት ለማገዝ ያደረጉት የትራክተር ድጋፍ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን ገልጸዋል።
ትራክተሮቹ የግብርናውን ልማት በማሳለጥ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ብለዋል።
በዓለም ምግብ ፕሮግራም የጋምቤላ ቅርንጫፍ ተጠሪ ሚስተር ኒክሰን ኡላንግ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ድርጅቱ ድጋፉን ያደረገው በክልሉ እየተካሄደ ያለውን የግብርና ልማት ሽግግር ለማገዝ ነው።
የጋምቤላ ብድርና ቁጠባ ተቋም ስራ አስኪያጅ አቶ ኡቻን ኡቻን በበኩላቸው፥ ድጋፉ ባህላዊ ግብርናን ወደ ዘመናዊ የግብርና ልማት ለማሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ጉሊህ ድርሻ አለው ብለዋል።
ትራክተሮቹ በዓለም ምግብ ፕሮግራም፣በመርሲ ኮርፕስና በክልሉ ብድርና ቁጠባ ተቋም ከ145 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገዙ ናቸው ተብሏል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026