የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የግብርናውን ልማት በሜካናይዜሽን በመደገፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የግብርናውን ልማት በሜካናይዜሽን በመደገፍ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።


በዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ "መርሲ ኮርፕስ"/Mercy Corps/ በተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅትና በጋምቤላ ብድርና ቁጠባ ተቋም ትብብር የተገዙ ዘጠኝ የእርሻ ትራክተሮች ለክልሉ ድጋፍ ተደርጓል።


ርዕሰ መስተዳደሯ በርክክቡ ላይ እንዳሉት፥ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋትና ልማቱን በማሳለጥ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተግተን እንሰራለን።


በተለይም በመጪው የመኸር እርሻ አንድም መሬት ጾም እንዳያድር የግብርና ልማቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ጠንክረን ልንሰራ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።


ርዕሰ መስተዳድሯ ለዓለም ምግብ ፕሮግራም፣መርሲ ኮርፕስ ለተሰኘ ግብር ሰናይ ድርጅት፣ ለክልሉ ብድርና ቁጠባ ተቋምና ለአኝዋሃ ልማት ማህበር ዘርፉን ለማገዝ ላደረጉት ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።


ምክትል ርዕሰ መስተደድሩ ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) በበኩላቸው፥በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመንና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የአጋር አካላት ድጋፋና ትብብር ወሳኝ ነው።


የክልሉ መንግስት ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመላቀቅ ሰፊ ጥረት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


በዓለም ምግብ ፕሮግራም፣መርሲ ኮርፕስ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርድት እና ከክልሉ ብድርና ቁጠባ ተቋም ጋር በመተባበር የክልሉን የግብርና ልማት ለማገዝ ያደረጉት የትራክተር ድጋፍ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን ገልጸዋል።


ትራክተሮቹ የግብርናውን ልማት በማሳለጥ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ የጎላ ፋይዳ ይኖራቸዋል ብለዋል።


በዓለም ምግብ ፕሮግራም የጋምቤላ ቅርንጫፍ ተጠሪ ሚስተር ኒክሰን ኡላንግ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ድርጅቱ ድጋፉን ያደረገው በክልሉ እየተካሄደ ያለውን የግብርና ልማት ሽግግር ለማገዝ ነው።


የጋምቤላ ብድርና ቁጠባ ተቋም ስራ አስኪያጅ አቶ ኡቻን ኡቻን በበኩላቸው፥ ድጋፉ ባህላዊ ግብርናን ወደ ዘመናዊ የግብርና ልማት ለማሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ጉሊህ ድርሻ አለው ብለዋል።


ትራክተሮቹ በዓለም ምግብ ፕሮግራም፣በመርሲ ኮርፕስና በክልሉ ብድርና ቁጠባ ተቋም ከ145 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገዙ ናቸው ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026