የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ ይሻል

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዳማ/ ቦንጋ/ አርባምንጭ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ የሚሻ መሆኑን በተለያዩ ከተሞች ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከባህር በቅርብ ርቀት ላይ ሆና የባህር በር ተነፍጓት ብትቆይም አሁን ላይ የሀገር የህልውና ጉዳይ እና የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ መነሳት ከጀመረ ውሎ አድሯል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ተደጋጋሚ ማብራሪያዎችን የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የበዛ ህዝብ ይዘን ተቆልፎብን መኖር ስለማንችል የባህር በር ጉዳይ የህልውና ጥያቄ መሆኑን በተደጋጋሚ አፅንኦት ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመደመር ትውልድ መፅሃፋቸው ላይም የባህር በር ጉዳይ ምላሽ የሚሻ የትውልዱ ጥያቄ መሆኑን ማስፈራቸው ይታወቃል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ በአዳማ፣ ቦንጋ እና አርባ ምንጭ ከተሞች ያነጋገራቸው ወጣቶች የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ የሚሻ መሆኑን ተናግረዋል።


የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪው ወጣት ተገኝ አበራ፣ የቦንጋ ከተማ ነዋሪው ወጣት አክሊሉ ሀይለማሪም እና የአዳማ ከተማ ነዋሪው ወጣት አቤሜሌክ አየለ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ ለሀገር የህልውና መሰረት ከመሆኑም በላይ የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ እንደሚሻ ገልጸዋል።


በዚህ ረገድ መንግስት ጥያቄውን አንስቶ ምላሽ እስከሚያገኝ ድረስ አጠናክሮ መቀጠሉን በማድነቅ ለስኬታማነቱ የድርሻችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል።

የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎቹ ወጣት ግሩምነሽ ሀጫ እና ወጣት ቀኝያለው ትዕዛዙ፤ የባህር በር ጥያቄው በሰጥቶ መቀበል መርህ በመንግስት የተጀመረው የዲፕሎማሲ ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የአሁኑ ትውልድ በመደመር መርህ ብሔራዊ ጥቅምን፣ ሀገራዊ ልማትና እድገትን አንግቦ እየሰራ መሆኑን ያነሱት ወጣቶቹ ቀጣይነት ያለው ጥረት እናደርጋለን ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊነትን ያነገበና የሀገር የህልውና ጉዳይ በመሆኑ የዲፕሎማሲ ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ መግለጻቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026