የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ ይሻል

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዳማ/ ቦንጋ/ አርባምንጭ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ የሚሻ መሆኑን በተለያዩ ከተሞች ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከባህር በቅርብ ርቀት ላይ ሆና የባህር በር ተነፍጓት ብትቆይም አሁን ላይ የሀገር የህልውና ጉዳይ እና የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ መነሳት ከጀመረ ውሎ አድሯል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ተደጋጋሚ ማብራሪያዎችን የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የበዛ ህዝብ ይዘን ተቆልፎብን መኖር ስለማንችል የባህር በር ጉዳይ የህልውና ጥያቄ መሆኑን በተደጋጋሚ አፅንኦት ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመደመር ትውልድ መፅሃፋቸው ላይም የባህር በር ጉዳይ ምላሽ የሚሻ የትውልዱ ጥያቄ መሆኑን ማስፈራቸው ይታወቃል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ በአዳማ፣ ቦንጋ እና አርባ ምንጭ ከተሞች ያነጋገራቸው ወጣቶች የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ የሀገር የህልውና መሰረትና የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ የሚሻ መሆኑን ተናግረዋል።


የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪው ወጣት ተገኝ አበራ፣ የቦንጋ ከተማ ነዋሪው ወጣት አክሊሉ ሀይለማሪም እና የአዳማ ከተማ ነዋሪው ወጣት አቤሜሌክ አየለ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ ለሀገር የህልውና መሰረት ከመሆኑም በላይ የትውልዱ ጥያቄ በመሆኑ ቀና ምላሽ እንደሚሻ ገልጸዋል።


በዚህ ረገድ መንግስት ጥያቄውን አንስቶ ምላሽ እስከሚያገኝ ድረስ አጠናክሮ መቀጠሉን በማድነቅ ለስኬታማነቱ የድርሻችንን ለመወጣት እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል።

የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎቹ ወጣት ግሩምነሽ ሀጫ እና ወጣት ቀኝያለው ትዕዛዙ፤ የባህር በር ጥያቄው በሰጥቶ መቀበል መርህ በመንግስት የተጀመረው የዲፕሎማሲ ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የአሁኑ ትውልድ በመደመር መርህ ብሔራዊ ጥቅምን፣ ሀገራዊ ልማትና እድገትን አንግቦ እየሰራ መሆኑን ያነሱት ወጣቶቹ ቀጣይነት ያለው ጥረት እናደርጋለን ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊነትን ያነገበና የሀገር የህልውና ጉዳይ በመሆኑ የዲፕሎማሲ ጥረቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ መግለጻቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026