የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

አዲስ አበባን ውብ እና ጽዱ በማድረግ ሂደት ላይ አሻራችንን በማኖራችን ኩራት ይሰማናል - የኮሪደር ልማት ሰራተኞች

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 2/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባን ውብ እና ጽዱ በማድረግ ሂደት ላይ አሻራችንን በማኖራችን ኩራት ይሰማናል ሲሉ የኮሪደር ልማት ሰራተኞች ገለጹ።

በመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የመንገድ፣ የመብራት፣ የቤት ግንባታ እና እድሳት እንዲሁም ሌሎች የልማት ተግባራትን በማከናወን መዲናዋን ትርጉም ባለው መልኩ ማስዋብ እና ማሳመር ተችሏል፡፡

የሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የወንዝ ዳር ልማቶችን ጨምሮ በስምንት የተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች በመፋጠን ላይ ይገኛል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመከናወን ላይ የሚገኘውን የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የስራ እንቅስቃሴ ትናንት ምሽት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ከንቲባዋ በኮሪደር ልማቱ እየተሳተፉ የሚገኙ ሰራተኞችን በማበረታታት የእራት ግብዣ አድርገዋል።

የልማት ስራዎቹን በተቀመጠላቸው ጊዜ እና ጥራት ለማጠናቀቅ ሳምንቱን ሙሉ ቀን ከሌት ስራው እየተከናወነ ይገኛል፡፡

በምሽት የኮሪደር ልማት እየተሳተፉ ከሚገኙ ሰራተኞች መካከል ሳሙዔል አዲሱ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት፤ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በስራ ቦታችን ተገኝተው ስላበረታቱን ከፍተኛ ደስታ ተስምቶናል ብሏል።

ጉብኝቱ ይበልጥ ለስራ እንዲበረቱና ልማቱን በተያዘለት እቅድ ለማጠናቀቅ እንዲተጉ የሞራል ስንቅ እንደሆናቸውም ገልጿል።

እኛም አዲስ አበባ ከተማን ውብ እና ጽዱ በማድረግ ሂደት ላይ አሻራችንን በማኖራችን ኩራት ይሰማናል ነው ያለው።

ሌላኛዋ የኮሪደር ልማት ሰራተኛ መዲካ ከበደ በበኩሏ፤ የኮሪደር ልማቱ ለእናቶች፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግራለች፡፡

ከንቲባዋም በየጊዜው እየመጡ ሰራተኞችን እንደሚያበረታቱ እና ድጋፍ እንደሚያደርጉላቸው አንስታለች።

አዲስ አበባ ከተማን ለማስዋብ በሚደረግ ጥረት የበኩሌን አስተዋጽኦ እየተወጣሁ በመሆኑ ክብርና ደስታ ይሰማኛል ያለችው ደግሞ ሌላዋ በኮሪደር ልማቱ ስራ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ሜላት አበበ ናት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025