የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አዲስ አበባን ውብ እና ጽዱ በማድረግ ሂደት ላይ አሻራችንን በማኖራችን ኩራት ይሰማናል - የኮሪደር ልማት ሰራተኞች

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 2/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባን ውብ እና ጽዱ በማድረግ ሂደት ላይ አሻራችንን በማኖራችን ኩራት ይሰማናል ሲሉ የኮሪደር ልማት ሰራተኞች ገለጹ።

በመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የመንገድ፣ የመብራት፣ የቤት ግንባታ እና እድሳት እንዲሁም ሌሎች የልማት ተግባራትን በማከናወን መዲናዋን ትርጉም ባለው መልኩ ማስዋብ እና ማሳመር ተችሏል፡፡

የሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የወንዝ ዳር ልማቶችን ጨምሮ በስምንት የተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች በመፋጠን ላይ ይገኛል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመከናወን ላይ የሚገኘውን የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የስራ እንቅስቃሴ ትናንት ምሽት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ከንቲባዋ በኮሪደር ልማቱ እየተሳተፉ የሚገኙ ሰራተኞችን በማበረታታት የእራት ግብዣ አድርገዋል።

የልማት ስራዎቹን በተቀመጠላቸው ጊዜ እና ጥራት ለማጠናቀቅ ሳምንቱን ሙሉ ቀን ከሌት ስራው እየተከናወነ ይገኛል፡፡

በምሽት የኮሪደር ልማት እየተሳተፉ ከሚገኙ ሰራተኞች መካከል ሳሙዔል አዲሱ ለኢዜአ በሰጠው አስተያየት፤ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በስራ ቦታችን ተገኝተው ስላበረታቱን ከፍተኛ ደስታ ተስምቶናል ብሏል።

ጉብኝቱ ይበልጥ ለስራ እንዲበረቱና ልማቱን በተያዘለት እቅድ ለማጠናቀቅ እንዲተጉ የሞራል ስንቅ እንደሆናቸውም ገልጿል።

እኛም አዲስ አበባ ከተማን ውብ እና ጽዱ በማድረግ ሂደት ላይ አሻራችንን በማኖራችን ኩራት ይሰማናል ነው ያለው።

ሌላኛዋ የኮሪደር ልማት ሰራተኛ መዲካ ከበደ በበኩሏ፤ የኮሪደር ልማቱ ለእናቶች፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግራለች፡፡

ከንቲባዋም በየጊዜው እየመጡ ሰራተኞችን እንደሚያበረታቱ እና ድጋፍ እንደሚያደርጉላቸው አንስታለች።

አዲስ አበባ ከተማን ለማስዋብ በሚደረግ ጥረት የበኩሌን አስተዋጽኦ እየተወጣሁ በመሆኑ ክብርና ደስታ ይሰማኛል ያለችው ደግሞ ሌላዋ በኮሪደር ልማቱ ስራ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ሜላት አበበ ናት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026