የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቷል

Apr 11, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017( ኢዜአ) ፡-በትግራይ ክልል በበጋ መስኖ በመጀመሪያው ዙር ከለማው መሬት 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱ ተገለፀ።

በበጋ መስኖ ልማቱ ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተሳታፊ መሆናቸውም ተገልጿል።

በጊዜያዊ አስተዳደሩ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የመስኖ ልማት ዳይሬክቶሬት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን አስተባባሪ አቶ ሀየሎም ተካ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ በመጀመሪያው ዙር በመስኖ ከለማው 58 ሺህ ሄክታር መሬት የ54 ሺህ ሄክታሩ የምርት ግምገማ ተጠናቋል።

በክልሉ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት አስካሁን በተሰበሰበው መረጃ 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ተናግረዋል።

በበጋ መስኖ የለማው አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎች እንደሚገኙባቸው የገለፁት አስተባባሪው ሁለተኛው ዙር የበጋ መስኖ ልማት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።


የአርሶ አደሩ የመስኖ ልማት ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን የተናገሩት አስተባባሪው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራታቸው፣ የግብዓት አቅርቦትና የባለሙያ ድጋፍ ታክሎበት የተሻለ ምርት ሊገኝ መቻሉን ገልፀዋል።

በዘንድሮው የመጀመሪያ ዙር የመስኖ ልማት ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልፀው ከዚህም ውስጥ 39 ሺህ 506ቱ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመስኖ ልማት የተሳተፉ አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት ሌሎች አርሶ አደሮችን ለተሳትፎ ማነሳሳቱንም አስተባባሪው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025