የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቷል

Apr 11, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017( ኢዜአ) ፡-በትግራይ ክልል በበጋ መስኖ በመጀመሪያው ዙር ከለማው መሬት 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱ ተገለፀ።

በበጋ መስኖ ልማቱ ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተሳታፊ መሆናቸውም ተገልጿል።

በጊዜያዊ አስተዳደሩ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የመስኖ ልማት ዳይሬክቶሬት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን አስተባባሪ አቶ ሀየሎም ተካ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ በመጀመሪያው ዙር በመስኖ ከለማው 58 ሺህ ሄክታር መሬት የ54 ሺህ ሄክታሩ የምርት ግምገማ ተጠናቋል።

በክልሉ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት አስካሁን በተሰበሰበው መረጃ 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ተናግረዋል።

በበጋ መስኖ የለማው አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎች እንደሚገኙባቸው የገለፁት አስተባባሪው ሁለተኛው ዙር የበጋ መስኖ ልማት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።


የአርሶ አደሩ የመስኖ ልማት ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን የተናገሩት አስተባባሪው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራታቸው፣ የግብዓት አቅርቦትና የባለሙያ ድጋፍ ታክሎበት የተሻለ ምርት ሊገኝ መቻሉን ገልፀዋል።

በዘንድሮው የመጀመሪያ ዙር የመስኖ ልማት ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልፀው ከዚህም ውስጥ 39 ሺህ 506ቱ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመስኖ ልማት የተሳተፉ አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት ሌሎች አርሶ አደሮችን ለተሳትፎ ማነሳሳቱንም አስተባባሪው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026