
መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017( ኢዜአ) ፡-በትግራይ ክልል በበጋ መስኖ በመጀመሪያው ዙር ከለማው መሬት 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱ ተገለፀ።
በበጋ መስኖ ልማቱ ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተሳታፊ መሆናቸውም ተገልጿል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የመስኖ ልማት ዳይሬክቶሬት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን አስተባባሪ አቶ ሀየሎም ተካ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ በመጀመሪያው ዙር በመስኖ ከለማው 58 ሺህ ሄክታር መሬት የ54 ሺህ ሄክታሩ የምርት ግምገማ ተጠናቋል።
በክልሉ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት አስካሁን በተሰበሰበው መረጃ 6 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ተናግረዋል።
በበጋ መስኖ የለማው አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎች እንደሚገኙባቸው የገለፁት አስተባባሪው ሁለተኛው ዙር የበጋ መስኖ ልማት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።

የአርሶ አደሩ የመስኖ ልማት ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን የተናገሩት አስተባባሪው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራታቸው፣ የግብዓት አቅርቦትና የባለሙያ ድጋፍ ታክሎበት የተሻለ ምርት ሊገኝ መቻሉን ገልፀዋል።
በዘንድሮው የመጀመሪያ ዙር የመስኖ ልማት ከ130 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልፀው ከዚህም ውስጥ 39 ሺህ 506ቱ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።
በመስኖ ልማት የተሳተፉ አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት ሌሎች አርሶ አደሮችን ለተሳትፎ ማነሳሳቱንም አስተባባሪው ገልፀዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026