
ዲላ፤ሚያዝያ 4/2017 (ኢዜአ) :-የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉባቸውን ማነቆዎች በመፍታት ውጤታማነታቸውን እንዲያረጋግጡ እየተደረገ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማና የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ተካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሐመድ እንዳሉት፥ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ግብርናን ከማዘመን ባለፈ ወደ ኢንዱስትሪ ለሚደረገው ሽግግር መሰረት ናቸው።

በሀገሪቱ የሚገኙ እነዚህ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች ምርቶች ላይ እሴት ጨምረው የማቀነባበር ሚናቸውን እንዲወጡና ውጤታማነታቸውን ለማረጋገጥ የሚገጥማቸውን ማነቆዎች መፍታትን ጨምሮ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ፓርኮቹ በተለይም የፋይናንስ፣ የኃይል አቅርቦትና የገበያ ትስስር ችግሮች መለየታቸውን ገልጸው፥ በተቀናጀ መንገድ በመፍታት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት የዲላና የይርጋጨፌ መካከለኛ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮችን በማስተዋወቅ አልሚ ባለሃብቱን በመሳቡ ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ያነሱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ ናቸው።

ፓርኮቹ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ተከናውኖላቸው ለምርት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በተለይ የዲላው ፓርክ የአቮካዶ ዘይት በማምረት በወጪ ንግድና በስራ ፈጠራ ረገድ ውጤታማ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።
በቀጣይ 90 ቀናት ወደ ፓርኩ ለመግባት ፍላጎት ያሳዩ 6 ባለሃብቶችን ስራ በማስጀመር የፓርኩን ውጤታማነት ለማጠናከር ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልጸዋል።
በመድረኩም ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ተገኝተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026