
ዲላ፤ሚያዝያ 4/2017 (ኢዜአ) :-የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉባቸውን ማነቆዎች በመፍታት ውጤታማነታቸውን እንዲያረጋግጡ እየተደረገ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማና የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ተካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሐመድ እንዳሉት፥ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ግብርናን ከማዘመን ባለፈ ወደ ኢንዱስትሪ ለሚደረገው ሽግግር መሰረት ናቸው።

በሀገሪቱ የሚገኙ እነዚህ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች ምርቶች ላይ እሴት ጨምረው የማቀነባበር ሚናቸውን እንዲወጡና ውጤታማነታቸውን ለማረጋገጥ የሚገጥማቸውን ማነቆዎች መፍታትን ጨምሮ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ፓርኮቹ በተለይም የፋይናንስ፣ የኃይል አቅርቦትና የገበያ ትስስር ችግሮች መለየታቸውን ገልጸው፥ በተቀናጀ መንገድ በመፍታት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት የዲላና የይርጋጨፌ መካከለኛ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮችን በማስተዋወቅ አልሚ ባለሃብቱን በመሳቡ ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ያነሱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ ናቸው።

ፓርኮቹ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ተከናውኖላቸው ለምርት ዝግጁ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በተለይ የዲላው ፓርክ የአቮካዶ ዘይት በማምረት በወጪ ንግድና በስራ ፈጠራ ረገድ ውጤታማ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።
በቀጣይ 90 ቀናት ወደ ፓርኩ ለመግባት ፍላጎት ያሳዩ 6 ባለሃብቶችን ስራ በማስጀመር የፓርኩን ውጤታማነት ለማጠናከር ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልጸዋል።
በመድረኩም ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ተገኝተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026