
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ) ፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸም 98 ነጥብ 66 በመቶ መድረሱን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የአፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ማካሄድ ጀምረዋል።
መርሃ ግብሩ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም አቅርቦትን በመመልከት የጀመረ ሲሆን ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያ በሀገር ውስጥ ኢኮኖሚ ላይ ያለው ተፅዕኖ አጠቃላይ ምልከታ ቀርቧል።
በመካሄድ ላይ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም እርምጃ ወቅታዊ መረጃ መቅረቡንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
የዓለም ኢኮኖሚ በ2025 በ3 ነጥብ 3 በመቶ የሚያድግ መሆኑ የተተነበየ መሆኑም የተገለጠ ሲሆን ከሰሃራ በታች ያለውን የአፍሪካ ክፍል ጨምሮ አብዛኛው የዓለም ክፍል አዎንታዊ እድገት እንደሚያስመዘግብ ተገልጧል።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 8.4 በመቶ እንደሚያድግ መተንበዩን ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም መርሃ ግብር የተረጋጋ ሆኖ የቁጠባ እና የኢንቨስትመንት እድገትም አሳይቷል።
የውጭ እዳ ከሀገራዊ የምርት መጠን(ጂዲፒ) ያለው ምጣኔ 13 ነጥብ 7 ከመቶ በመድረስ ትርጉም ባለው መጠን መቀነሱ ተገልጿል።
በተጨማሪም አዲስ የውጭ ምንዛሬ አሰራር መዘርጋቱም ከውጭ የሚላክ የውጭ ምንዛሪ እንዲጨምር በማድረግ የኢትዮጵያን የውጪ ምንዛሬ ክምችት መጨመሩም እንዲሁ።
ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም ከግብርና፣ ከማዕድን፣ ከኢንደስትሪ እና ኤሌክትሪክ የተገኙ የውጭ ንግድ ገቢዎችም እድገት ማሳየታቸው በግምገማው ወቅት ተገልጿል።
ቡና፣ ወርቅ፣ ጥራጥሬ፣ የዘይት ምንጭ ፍሬዎች፣ አበባ እና ኤሌክትሪክ አምስቱ ቀዳሚ የውጭ ንግድ ምርቶች መሆናቸውም ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል ግምገማው ታላላቅ የመሠረተ ልማት እና ሌሎች ታላላቅ ፕሮጀክቶችንም አፈፃፀም ተመልክቷል።
ለአብነትም የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ 98 ነጥብ 66 ከመቶ አፈፃፀም ላይ የደረሰ ሲሆን ስድስት ዩኒቶቹም ወደ ስራ መግባታቸው የጽህፈት ቤቱ መረጃ ያሳያል።
ዛሬ ጠዋት የነበረው ግምገማ የዘላቂ የልማት ጥረቶች በተለይም አካታችነትን እንደ ቁልፍ የስኬት መለኪያ በመውስድ በመመልከት ተጠናቋል።
ለዘላቂ ልማት ሥራ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ የሥራ ተግባራትም መቅረባቸው ተመላክቷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026