
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ) ፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸም 98 ነጥብ 66 በመቶ መድረሱን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የአፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ማካሄድ ጀምረዋል።
መርሃ ግብሩ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም አቅርቦትን በመመልከት የጀመረ ሲሆን ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያ በሀገር ውስጥ ኢኮኖሚ ላይ ያለው ተፅዕኖ አጠቃላይ ምልከታ ቀርቧል።
በመካሄድ ላይ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም እርምጃ ወቅታዊ መረጃ መቅረቡንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
የዓለም ኢኮኖሚ በ2025 በ3 ነጥብ 3 በመቶ የሚያድግ መሆኑ የተተነበየ መሆኑም የተገለጠ ሲሆን ከሰሃራ በታች ያለውን የአፍሪካ ክፍል ጨምሮ አብዛኛው የዓለም ክፍል አዎንታዊ እድገት እንደሚያስመዘግብ ተገልጧል።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 8.4 በመቶ እንደሚያድግ መተንበዩን ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።
የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም መርሃ ግብር የተረጋጋ ሆኖ የቁጠባ እና የኢንቨስትመንት እድገትም አሳይቷል።
የውጭ እዳ ከሀገራዊ የምርት መጠን(ጂዲፒ) ያለው ምጣኔ 13 ነጥብ 7 ከመቶ በመድረስ ትርጉም ባለው መጠን መቀነሱ ተገልጿል።
በተጨማሪም አዲስ የውጭ ምንዛሬ አሰራር መዘርጋቱም ከውጭ የሚላክ የውጭ ምንዛሪ እንዲጨምር በማድረግ የኢትዮጵያን የውጪ ምንዛሬ ክምችት መጨመሩም እንዲሁ።
ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም ከግብርና፣ ከማዕድን፣ ከኢንደስትሪ እና ኤሌክትሪክ የተገኙ የውጭ ንግድ ገቢዎችም እድገት ማሳየታቸው በግምገማው ወቅት ተገልጿል።
ቡና፣ ወርቅ፣ ጥራጥሬ፣ የዘይት ምንጭ ፍሬዎች፣ አበባ እና ኤሌክትሪክ አምስቱ ቀዳሚ የውጭ ንግድ ምርቶች መሆናቸውም ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል ግምገማው ታላላቅ የመሠረተ ልማት እና ሌሎች ታላላቅ ፕሮጀክቶችንም አፈፃፀም ተመልክቷል።
ለአብነትም የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ 98 ነጥብ 66 ከመቶ አፈፃፀም ላይ የደረሰ ሲሆን ስድስት ዩኒቶቹም ወደ ስራ መግባታቸው የጽህፈት ቤቱ መረጃ ያሳያል።
ዛሬ ጠዋት የነበረው ግምገማ የዘላቂ የልማት ጥረቶች በተለይም አካታችነትን እንደ ቁልፍ የስኬት መለኪያ በመውስድ በመመልከት ተጠናቋል።
ለዘላቂ ልማት ሥራ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ የሥራ ተግባራትም መቅረባቸው ተመላክቷል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026