
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ።

የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ኃላፊው አቶ እንድሪስ አህመድ ገልጸዋል።
በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን ኤር ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ወደ ጋዝ ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ብሬከር የመቀየር ሥራ መሰራቱ የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
የብሬከር ቅየራው አሁን ላይ 70 በመቶ መድረሱንና ሲጠናቀቅ የጣቢያውን ኃይል የማቅረብ አቅም አስተማማኝና የተቀላጠፈ እንደሚያደርገውም መናገራቸውን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ለሰመራ፣ ለሎጊያ፣ ለሚሌ፣ ለአሳይታ፣ ለዱብቲ ከተሞችና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ ያስችላል ያሉት ደግሞ የሪጅኑ ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሙሀመድ አብዱ ናቸው።
የሰመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከኮምቦልቻ በ230 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል ወደ አፍዴራና ዲቾቶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በማስተላለፍ ከ80 በመቶ በላይ የሆነውን የአፋር ክልል ተደራሽ ያደርጋል ብለዋል።
አንድ ገቢ መስመርና ሁለት ወጪ መስመሮች ያሉት የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ በ2003 ዓ.ም ተገንብቶ ለክልሉ በዋነኛነት ኃይል በማቅረብ እያገለገለ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026