
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ።

የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ኃላፊው አቶ እንድሪስ አህመድ ገልጸዋል።
በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን ኤር ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ወደ ጋዝ ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ብሬከር የመቀየር ሥራ መሰራቱ የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
የብሬከር ቅየራው አሁን ላይ 70 በመቶ መድረሱንና ሲጠናቀቅ የጣቢያውን ኃይል የማቅረብ አቅም አስተማማኝና የተቀላጠፈ እንደሚያደርገውም መናገራቸውን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ለሰመራ፣ ለሎጊያ፣ ለሚሌ፣ ለአሳይታ፣ ለዱብቲ ከተሞችና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ ያስችላል ያሉት ደግሞ የሪጅኑ ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሙሀመድ አብዱ ናቸው።
የሰመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከኮምቦልቻ በ230 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል ወደ አፍዴራና ዲቾቶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በማስተላለፍ ከ80 በመቶ በላይ የሆነውን የአፋር ክልል ተደራሽ ያደርጋል ብለዋል።
አንድ ገቢ መስመርና ሁለት ወጪ መስመሮች ያሉት የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ በ2003 ዓ.ም ተገንብቶ ለክልሉ በዋነኛነት ኃይል በማቅረብ እያገለገለ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026