የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የቡናና ቅመማቅመም አመራረት ፓኬጆችን በማሻሻል የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

Apr 15, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣ ሚያዚያ 6/2017 (ኢዜአ):- የቡናና ቅመማም አመራረት ፓኬጆችን በማሻሻል የዘርፉን አኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ከምርምር ማዕከላት ጋር በመተባበር የተሻሻሉ የቡናና ቅመማ ቅመም ፓኬጆች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከምዕራብ ኦሮሚያ ዞኖች፣ ጋምቤላ እና ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ለተወጣጡ የዘርፉ ከፍተኛ ባለሙያዎች በሚዛን አማን ከተማ እየሰጠ ነው።

ስልጠናው የዘርፉ ባለሙያዎች የቡናን ምርታማነት በጥራት ለማከናወን የተቀረጹ ፓኬጆች ላይ በቂ ግንዛቤ በመያዝ አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ያለመ ነው ብለዋል።


በባለሥልጣኑ የሻይና ቡና ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ደፈረስ እንዳሉት ኢትዮጵያ ለቡናና ቅመማ ቅመም ያላትን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ለማድረግ ጠንክሮ መሥራት ያስፈልጋል።

ለዚህም ባለሥልጣኑ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ፓኬጆችን በመንደፍ ለአርሶ አደሩ የማስተዋወቅ ተግባር እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የዘርፉን ባለሙያዎች ክህሎት ለማሳደግ በተለያዩ ጊዜያት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አንስተው የአሁኑም ስልጠና የዚሁ አካል መሆኑን አመልክተዋል።

የአርሶ አደሩን ምርታማነትን ማሳደግ የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መሠረት እንደሚጥልም ጠቁመዋል።


የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አሥራት መኩሪያ ክልሉ ለቡና ልማት ያለውን ተስማሚነት በመጠቀም ሽፋኑን ለማሳደግ እየሠራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ከ582 ሺህ ሄክታር በላይ የቡና ማሳ መኖሩን ጠቅሰው የግብይት ምጣኔን ከፍ ለማድረግ የባለ ልዩ ጣዕም ቡናናን የጥራት ደረጃ ለማሻሻል ትኩረት መደረጉን ገልጸዋል።

ከቡና ባሻገር ከ90 ሺህ ሄክታር በላይ ቅመማ ቅመምና ከ2 ሺህ 300 ሄክታር በላይ የሻይ ልማት መኖሩን ጠቅሰዋል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አማካሪ አቶ ዮሐንስ መላኩ በበኩላቸው በቡና ምርታማነትና ጥራት ላይ በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ሊያደርጉን የሚችሉ አስፈላጊ የአመራረት ማሻሻያ ሥራዎችን ለአርሶ አደሩ ማቅረብ ይገባል ብለዋል።

ምርታማነቱንም በሄክታር ያለውን ልዩነት ወጥ በሆነ የአመራረት ዘዴ ለማጥበብ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

ክልሉ ከቡና ባሻገር ለቁንዶ በርበሬ፣ ኮረሪማ፣ ዝንጅብልና ሌሎች የቅመማ ቅመም ምርቶች ምቹ ሥነ ምህዳር ያለው በመሆኑ ተጨባጭ ውጤት ከዘርፉ ለማምጣት ይሠራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026