
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፡-አፍሪካ በዌልዲንግ ዘርፍ ያላትን ትልቅ አቅም ለመጠቀም የሀገራት የጋራ ስራ ሊጠናከር እንደሚገባ የፌዴራል ቴክኒክ ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ከሚያዝያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ሶስተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ዓመታዊ ጉባኤና ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መርሃ-ግብር ተካሄዷል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ሐመድ አቡደል አሊም፣የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
የፌዴራል ቴክኒክ ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፥ ጉባኤው ስኬታማ ነበር።
በጉባኤው ለዌልዲንግ ዘርፍ ስኬታማነት አስተዋፅኦ የሚያደርጉ ፍሬያማ ውይይቶች የተደረጉበት እንዲሁም አፍሪካ በብየዳ ሙያ ያላትን ትልቅ አቅም ያሳየችበት መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የአፍሪካ ሀገራት ትስስራቸውን በማጠናከር ዘርፉን በጋራ ለማሳደግ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋገጡበት ነው ብለዋል።

የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ሐመድ አቡደል አሊም፥ ኢትዮጵያ ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት ሰጥታ ጉባኤውን በተደራጀ ሁኔታ በማዘጋጀቷ ምስጋናቸውን ገልጸዋል።
ጉባኤው በአህጉሪቱ ስላለው የዌልዲንግ አቅም ግንዛቤ የተፈጠረበት፣ ዘርፉን ለማጠናከር ትምህርት የተገኘበትና በጋራ መስራት እንደሚገባ መግባባት የተደረሰበት መሆኑን አመልክተዋል፡፡
በጉባኤው አፍሪካውያን የዌልዲንግ ልምዳቸውን የተለዋወጡበትና በዘርፉ ተጨማሪ እውቀት የቀሰሙበት መሆኑን የተናገረችው በጉባኤው የተሳተፈችው ደቡብ አፍሪካዊቷ ኮንፊዲ ሎኮንዴ ናት፡፡

ጉባኤው የዌልዲንግ ባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ በኩል ወሳኝ እንደነበር በማንሳት፥ ኩባንያዎች በዘርፉ መዋዕለ ንዋያቸውን ፈሰስ በማድረግ ለዘርፉ ዕድገት እንዲሰሩም ጠይቃለች።
በጉባኤው በተካሄዱ ውድድሮች ያሸነፉ ግለሰቦች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን፥ አራተኛውን የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ጉባኤ ደቡብ አፍሪካ እንደምታስተናግድ ታውቋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026