ባህርዳር፤ ሚያዚያ9/2017(ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከአልማ እስከ ዋተር ፍሮንት ሆቴል የሚካሄድ ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በተገኙበት የተጀመረው የፕሮጀክቱ ግንባታ 800 ሜትር ርዝመትና 40 ሜትር ስፋት ያለው አስፋልት መንገድ እንደሆነ ተመልክቷል።
መንገዱ ጣና ሀይቅን በቀጥታ ከከተማው የሚያገናኙ ከመሆኑም በላይ የከተማዋን ውበት፣ የቱሪስትና የኢንቨስትመንት ማዕከልነት ይበልጥ የሚያሳድግ እንደሆነ በሥነ-ሥርዓቱ ለይ ተነግሯል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የ3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ እየተፋጠነ ሲሆን በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
የኮሪደር ልማቱ የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛ መንገድ፣ የብስክሌት መንገድና ሌሎች ልማቶችን አካቶ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።
በማስጀመሪያው ሥነ-ሥርዓቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማውን ጨምሮ ሌሎች አመራር አባላትና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025