
ባህርዳር፤ ሚያዚያ9/2017(ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከአልማ እስከ ዋተር ፍሮንት ሆቴል የሚካሄድ ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በተገኙበት የተጀመረው የፕሮጀክቱ ግንባታ 800 ሜትር ርዝመትና 40 ሜትር ስፋት ያለው አስፋልት መንገድ እንደሆነ ተመልክቷል።

መንገዱ ጣና ሀይቅን በቀጥታ ከከተማው የሚያገናኙ ከመሆኑም በላይ የከተማዋን ውበት፣ የቱሪስትና የኢንቨስትመንት ማዕከልነት ይበልጥ የሚያሳድግ እንደሆነ በሥነ-ሥርዓቱ ለይ ተነግሯል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የ3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ እየተፋጠነ ሲሆን በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
የኮሪደር ልማቱ የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛ መንገድ፣ የብስክሌት መንገድና ሌሎች ልማቶችን አካቶ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።
በማስጀመሪያው ሥነ-ሥርዓቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማውን ጨምሮ ሌሎች አመራር አባላትና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026