
ባህርዳር፤ ሚያዚያ9/2017(ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከአልማ እስከ ዋተር ፍሮንት ሆቴል የሚካሄድ ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ዛሬ ተጀምሯል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በተገኙበት የተጀመረው የፕሮጀክቱ ግንባታ 800 ሜትር ርዝመትና 40 ሜትር ስፋት ያለው አስፋልት መንገድ እንደሆነ ተመልክቷል።

መንገዱ ጣና ሀይቅን በቀጥታ ከከተማው የሚያገናኙ ከመሆኑም በላይ የከተማዋን ውበት፣ የቱሪስትና የኢንቨስትመንት ማዕከልነት ይበልጥ የሚያሳድግ እንደሆነ በሥነ-ሥርዓቱ ለይ ተነግሯል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የ3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ እየተፋጠነ ሲሆን በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
የኮሪደር ልማቱ የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛ መንገድ፣ የብስክሌት መንገድና ሌሎች ልማቶችን አካቶ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።
በማስጀመሪያው ሥነ-ሥርዓቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማውን ጨምሮ ሌሎች አመራር አባላትና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026